የሕወሓት ህገወጥ ቡድን በአክሱም አውሮፕላን ማረፊያ ላይ ጉዳት ማድረሱ ተጠቆመ።
የቱሪስት መዳረሻ በሆነችው የአክሱም ከተማ የተገነባው የአውሮፕላን ማረፊያ በ526 ሚሊዮን 860 ሺህ 200 ብር ወጪ የተገነባ መሆኑን፣ ለአካባቢው ማህበረሰብና ለአገር ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅሙ ሰፊ የሆነው የአየር ማረፊያ መጎዳቱ፣ የአክሱም ሐውልትን ከጉዳት ለመታደግ የሚደረገውን የጥገና ስራ እንደሚያስተጓጉልና በርካታ ችግር ሊያስከትል እንደሚችል የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ዘግቧል።
አውሮፕላን ማረፊያው በቱሪስቶች የሚታወቅ፣ በቀንና በምሽት የተሟላ አገልግሎት እንደሚሰጥ ይታወቃል።