Sunday, June 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅየካንሰር ሕሙማንን መታደግ

የካንሰር ሕሙማንን መታደግ

ቀን:

በኢትዮጵያ የካንሰር ሕሙማን ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ ቢመጣም፣ የሕክምና አገልግሎቱ እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ በተለይ ለካንሰር ሕክምና ከሚያስፈልጉት አንዱ የሆነው የጨረር ሕክምናን ለማግኘት እስከ ዓመት የሚዘልቅ ወረፋ መጠበቅ ግድ ይላል፡፡ በዚህ መሀል በርካቶች ሕይወታቸውን ያጣሉ፡፡ ጤና ሚኒስቴር ችግሩን ለመቅረፍ አዲስ አበባን ጨምሮ በስድስት ሥፍራዎች የጨረር ሕክምናን ለማስፋፋት እየሠራ ይገኛል፡፡ ካለፉት 20 ዓመታት ወዲህ ብቸኛ ሆኖ የጨረር ሕክምና እየሰጠ የሚገኘው ጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በሁለት ማሽኖች እየሠራ የነበረ ቢሆንም፣ አንዱ በመበላሸቱ በአንድ ማሽን ብቻ እንዲሠራ ተገዷል፡፡ ችግሩን ለማቃለል አዲስ ሊነር አክስለሬተር (የጨረር መሣሪያ) አስገብቶ ሥራ አስጀምሯል፡፡ ኅዳር 21 ቀን 2013 ዓ.ም. የማሽኑ በይፋ ሥራ መጀመር የተገለጸ ሲሆን፣ በሥነ ሥርዓቱ ላይም የጤና ሚኒስትሯ ሊያ ታደሰ (ዶ/ር)፣ የቀድሞ ቀዳማዊት እመቤት ሮማን ተስፋዬ፣ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል የካንሰር ሕክምና ማዕከል ኃላፊ አይናለም አብርሃም (ዶ/ር) እና የሚመለከታቸው አካላት ተገኝተዋል፡፡

የካንሰር ሕሙማንን

የካንሰር ሕሙማንን

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

አወዛጋቢው የሕገ መንግሥት ማሻሻያ ጉዳይ

በኢትዮጵያ የሕገ መንግሥት ማሻሻል ጉዳይ ከፍተኛ የፖለቲካ ውዝግብ የሚቀሰቀስበት...

 መፍትሔ  ያላዘለው  የጎዳና  መደብሮችን  ማፍረስ

በአበበ ፍቅር ያለፉት ስድስት ዓመታት በርካቶች በግጭቶችና በመፈናቀሎች በከፍተኛ ሁኔታ...

የተናደው ከቀደምቱ አንዱ የነበረው የአዲስ አበባ ታሪካዊ ሕንፃ

ዳግማዊ አፄ ምኒልክ በ19ኛው ክፍለ ዘመን መገባደጃ መናገሻ ከተማቸውን...

የአከርካሪ አጥንት ሕክምናን ከፍ ያደረገው ‘ካይሮፕራክቲክ’

በአፍሪካ ከጀርባ ሕመም ጋር በተያያዘ በርካታ ሰዎች ለከፍተኛ የአካል...