Friday, June 9, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ሚኒስትሩ በጠዋት ቢሮ እንደገቡ ዘወትር እንደሚያደርጉት አማካሪያቸው የሚያቀርበውን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሪፖርት በመገረም እያደመጡ ነው]

  • እና በመቀሌ ከተማ ተገኝተዋል ነው የምትለኝ?
  • እርስዎ መረጃው አልነበረዎትም ነበር?
  • በጭራሽ አልሰማሁም። እርግጠኛ ነህ ግን?
  • መረጃዎቹ የሚያመለክቱት መቀሌ ተገኝተው ከጦር ጄኔራሎቹ ጋር መምከራቸውን ነው። አብረውም ፎቶ ተነስተዋል?
  • እስኪ ፎቶ ግራፉን አሳየኝ?
  • ይኽው. . .  
  • በፎቶ ሾፕ የተሠራ አለመሆኑን እርግጠኛ ነህ?
  • መቀሌ መሄድ እየተቻለ ለምን በፎቶ ሾፕ ማስመሰል ያስፈልጋል?
  • እንዴ ይኸው . . . ፎቶ ሾፕ ነው።
  • እንዴት አወቁ?
  • ተመልከት. . . አሁን የሚፈለጉት ሰዎች የተሰበሰቡበትን አዳራሽና ይኼኛውን አዳራሽ ተመልከት።
  • እየተመለከትኩት ነው ግን ሊያሳዩኝ የፈለጉት አልገባኝም?
  • አዳራሾቹ አንድ ዓይነት አለመሆናቸው አይታይህም? 
  • አዎ አንድ አይደሉም፡፡
  • አየህ ፎቶ ሾፕ ነው አላልኩህም? ስለዚህ አልሄዱም ማለት ነው።
  • ተሳስተዋል ክቡር ሚንስትር፡፡ 
  • ምን ላይ ነው የተሳሳትኩት?
  • አንድ አዳራሽ ይሰበሰባሉ ብለው ሲያስቡ ሐሳብዎን ሲያምኑ ነው የተሳሳቱት። 
  • እና የት ሊሰበሰቡ ይችላሉ? 
  • ብዙ መሰብሰቢያዎች እያሉ እንዴት እርስዎ ያሉት ቦታ ሊሰበሰቡ ይችላሉ? 
  • እኮ ሌላ የት አለ? 
  • ለምሳሌ ሰሜን ዕዝ አዳራሽ አለ፡፡
  •  በጠላት ቡድን ተይዞ የለም እንዴ እሱ?
  • አሃ. . . እርስዎ ገና አልገቡም ማለት ነው?
  • የት?
  • መቀሌ፡፡
  • ምን ማለትህ ነው?
  • መከላከያ ሠራዊት መቀሌን ከተቆጣጠረ ቆዬ ብዬ ነው።
  • እኔን ያሳሰበኝ ዋና ነገር እሱ አይደለም።
  • ምንድ ነው? 
  • እንዴት እኔ ወደ መቀሌ መሄዳቸውን አላወቅኩም፡፡ እንዴት አልተነገረኝም? 
  • እርስዎ ወጣ ሲሉ ይሆናል እነሱ የገቡት፡፡
  • ወዴት ወጣ አልኩ?
  • ቆላ ተምቤን
  • ሂድ ውጣልኝ! 

[ሚኒስትሩ በመኖሪያ ቤታቸው ከባለቤታቸው ጋር የምሽቱን የቴሌቪዥን ዜና እየተከታተሉ ሳለ አለቃቸው ከጦር ጄኔራሎች ጋር እየመከሩ የሚያሳየው የምስል ዜና መቅረብ ጀመረ]

  • እስኪ ወደ ሌላ ቻናል ቀይሪው?
  • እንዴ. . . ቆይ እንጂ. . . ዩኒፎርሙ ደግሞ እንዴት ያምርባቸዋል ባክህ. . . የት ሄደው ነው?
  • መቀሌ ነበሩ፡፡
  • ጠዋት እዚሁ ከውጭ የመጣ እንግዳ ሲቀበሉ አልነበረም እንዴ?
  • ከተቀበሉ በኋላ ሄዱ፡፡
  • ምሣ ላይ እንዴት አላወራኸኝም?
  • ንዳንድ መረጃዎች ለማንም እንደማይነገሩ አታውቂም?
  • አንተ የካቢኔ አባል አይደለህ እንዴት አይነግሩህም?
  • እኔማ አውቃለሁ።
  • እና የሚደበቀው ከማን ነው?
  • ለአንቺ ያልነገርኩሽ በሚስጥር መያዝ ስለነበረበት ነው ማለቴ ነው። 
  • አንተ ሰምተህ ለኔ ሳትነግረኝ?
  • ምንም ማድረግ አልችልም ነበር። 
  • ከዚህ የበለጡ ስንት ሚስጥሮች ያልደበቅከኝ ይኼንን ሚስጥር አደረግከው? 
  • አንዳንድ መረጃዎች ጥብቅ ናቸው ወጥተው ቢገኙ ያስጠይቀናል።
  • ቢሆንም ስንቱን ሚስጥር ስታወጋኝ ከርመህ? እኔ ደብቀኸኝ ነው ብዬ አላምንም። ሌላ ነገር እንዳይሆን?
  • ምን ሊሆን ይችላል?
  • ካንተም የተደበቀ ሚስጥር እንዳይሆን?
  • ምን ማለትሽ ነው የካቤኔ አባል አይደለሁ እንዴ? 
  • እሱማ ነህ ግን. . .  
  • ግን ምን?
  • ይኼ የካቢኔ ስብሰባ አይደለማ?
  • እና ቢሆንስ እኔ ማወቅ የለብኝም?
  • አሃ. . .  እነሱን ጠይቅ እንጂ እኔ ምን አውቃለሁ?
  • አጥፊልኝ አሁን ይኼንን ቴሌቪዥን!

[ክቡር ሚኒስትሩ በኢኮኖሚ ጉዳዮች ላይ ለመምከር የተጠራው ከፍተኛ የባለሙያዎች ስብሰባ ከመጀመሩ በፊት ከአንድ የባንክ ፕሬዝዳንት ጋር እየተወያዩ ነው]

  • ለውጡ ከተጀመረ ወዲህ ከሠራናቸው ስኬታማ ሥራዎች አንዱ የኢኮኖሚ ዘርፉ ነው። ለሌላውም ተምሳሌት የሚሆን ሥራ ይመስለኛል። 
  • ስኬት ለማለት አያስቸግርም ክቡር ሚኒስትር?
  • ለምን? ሌላውን ተወውና የብር ቅያሬው ስኬት ብቻ ተምሳሌት አይሆንም?
  • የብር ኖቶቹ መቀየራቸው ጥሩ ቢሆንም ስኬታማ ነው ማለት አይቻልም።
  • እንዴት? 
  • ገና አሮጌው ብር ተቀይሮ ሳያልቅ እየሆነ ያለውን እያዩት አይደል እንዴ?
  • ምን ሆነ?
  • የአዲሶቹ ብሮች ፎርጂድ በየቀኑ እየተያዙ ነው። ብሔራዊ ባንክም ከፎርጅድ ብሮች ተጠንቀቁ እያለ ነው።
  • ያሳዝናል ግን በለውጥ ላይ የሚገኝ አገር ከሚገጥሙት ፈተናዎች አንዱ እንዲህ ዓይነቱ ነው። 
  • እንዴት? 
  • የፖለቲካና የኢኮኖሚ ማዕከሉን አሳሳቾችና አጭበርባሪዎች ለመቆጣጠር በሚያደርጉት ፈተና መወዛወዝ ይበዛበታል። 
  • ታዲያ ዘፈኑን በመቀየር መያዝ አይሻልም?
  • ማንን?
  • ተወዛዋዦቹን!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅን የሚተካ ረቂቅ ተዘጋጀ

ከቫት ነፃ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ገደብ ተቀመጠለት የገንዘብ ሚኒስቴር ከሃያ...

መንበሩ ካለመወረሱ በስተቀር መፈንቅለ ሲኖዶስ መደረጉን ቤተ ክህነት አስታወቀ

ቅዱስ ሲኖዶስ ከነገ ጀምሮ ውይይት እንደሚጀምር ተነገረ ‹‹እኛ ወታደርም ሆነ...

ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኝ የባቡር መስመር ለመገንባት የሚያስችል የአዋጭነት ጥናት ተጠናቆ ለውይይት ቀረበ

ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኝ የባቡር መስመር ለመገንባት በሁለቱ አገሮች የተያዘውን...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ወልቃይትን ማዕከል ያደረገው የምዕራባዊያን ጫና

በትግራይ ክልል የተከሰተው የዕርዳታ እህል ዘረፋ የዓለም አቀፍ ተቋማት...

ከቀጣዩ ዓመት በጀት ውስጥ 281 ቢሊዮን ብሩ የበጀት ጉደለት ነው ተባለ

ለቀጣዩ በጀት ዓመት ከቀረበው 801.65 ቢሊዮን ብር አጠቃላይ በጀት...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

የባንክ ማቋቋሚያ መሥፈርት እንደሚጠነክር ሚኒስትሩ ተናገሩ

 ባንኮች ስለውህደት እንዲያስቡም መክረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ለማቋቋም የሚያስፈልገው መሥፈርት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አመሻሹን መኖሪያ ቤታቸው ሲደርሱ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈው የማዕከላዊ ኮሚቴ ገለጻ እየተከታተሉ አገኟቸውና አጠገባቸው ተቀምጠው የደረሱበትን አብረው መከታተል እንደጀመሩ፣ ባለቤታቸው ቴሌቪዥኑን ትተው መጠየቅ...

እኔ ምለው? እሺ... አንቺ የምትይው? የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ አባላት እንዲያወሩ ወይም እንዲጠይቁ አይፈቀድም እንዴ? እንዴት ይከለከላል? ታዲያ ለምንድነው ፕሬዚዳንቱ ብቻ የሚያወሩት? እያወሩ አይደለም፣ ገለጻ እያደረጉ ነው። ቢሆንም አንድም አባል...

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...