Monday, May 29, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናጣሊያን ኤምባሲ ለ30 ዓመታት የቆዩት ሌፍቴናንት ጀነራል አዲስ ተድላና ኮሎኔል...

ጣሊያን ኤምባሲ ለ30 ዓመታት የቆዩት ሌፍቴናንት ጀነራል አዲስ ተድላና ኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ በአመክሮ ከእስር እንዲፈቱ ፍርድ ቤት ትእዛዝ ሰጠ

ቀን:

የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም የክስ መዝገብ ተከሰው በሌሉበት ሞት ተፈርዶባቸው የነበሩትና ላለፉት 30ዓመታት  በጣሊያን ኤምባሲ ቅጥር ግቢ ውስጥ በጥበቃ ስር የነበሩት ሌፍቴናንት ጀነራል አዲስ ተድላና ኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ በአመክሮ እንዲፈቱ  ትእዛዝ ሰጠ።

ዛሬ የቀረበለትን የተዘጋ መዝገብና የአመክሮ ጥያቄ የተመለከተው ፍርድ ቤት፣  ሁለቱ የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ከጣሊያን ኤምባሲ በአመክሮ እንዲለቀቁ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ለፌዴራል ጠቅላይ አቃቤ ሕግና ለፌዴራል ፖሊስ ኮሚሽን ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡

ትዕዛዙ በኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በኩል ለጣሊያን ኤምባሲ፣ እንዲሁም ሌፍቴናንት ጀነራል አዲስ ተድላና ለኮሎኔል ብርሃኑ ባየህ እንዲደርስም ፍርድ ቤቱ አዟል፡፡

ሁለቱም የደርግ ከፍተኛ ባለስልጣናት ላይ የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው የነበረ ሲሆን፣ በኢፌዴሪ ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ  የሞት ፍርዱን ወደ እድሜ ልክ እስራት እንዲቀየርላቸው በማድረጋቸውና ዕድሜ ልክ እስር የተፈረደበት ሰው ደግሞ በአመክሮ መፈታት የሚችለው 20 ዓመት  ውስጥ  እስር ላይ መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ፍርድ ቤቱ ከእስር እንዲፈቱ ትእዛዝ ሰጥቷል።
ሁለቱ የደርግ ባለስልጣናት የፍርድ ቅጣታቸውን በወህኒቤት ታስረው ባይፈጽሙም ፣በጣሊያን ኤምባሲ ያሳለፉትየ30ዓመታት ጊዜ እንደ እስር ቅጣት ተቆጥሮ የአመክሮ መብታቸው እንዲከበር ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በቀረበው ማመልከቻ መሠረት፣ ፍርድ ቤቱ  በአመክሮ  እንዲለቀቁ መወሰኑን ሪፖርተር ለማወቅ ችሏል።

 

Bid

 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመስቀል አደባባይ የመግቢያ ክፍያ ለምን?

ወጣቶች፣ ሕፃናትና አረጋውያን ሳይቀሩ መንፈሳቸውን የሚያድሱበት እንዲሁም ሐሳባቸውን በነፃነት...

በሕገ መንግሥቱ የተዋቀረው ‹‹የብሔር ፖለቲካ›› እና ‹‹ሥርዓቱ›› ያስከተለው መዘዝና መፍትሔው

(ክፍል አራት) በዓቢዩ ብርሌ (ጌራ) ባለፈው ጽሑፌ (በክፍል ሦስት) አሁን ያለው...

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብና የመንግሥት መሪ ምሥል

በበቀለ ሹሜ በ2015 ዓ.ም. መጋቢት ወር ውስጥ ይመስለኛል በ‹ሸገር ካፌ›...

ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ያደረገው አዋጅ የፍትሐዊነት ጥያቄ አስነሳ

በቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት ስምንት ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ በማድረግ ተቋማዊና...