Tuesday, November 28, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ተከስቶ የነበረው የበረሃ አንበጣ ወረርሽኝ የ3.8 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ቅናሽ ሊያመጣ እንደሚችል ተጠቆመ

ተዛማጅ ፅሁፎች

በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ተከሰቶ የነበረው የበረሃ አንበጣ ወረርሽኝ በተያዘውመት ይገኛል ከተባለው አጠቃላይ 384 ሚሊዮን ኩንታል የሰብል ምርት ውስጥ፣ እስከ አንድ በመቶ ወይም 3.8 ሚሊዮን ኩንታል ያህል ቅናሽ ሊያመጣ እንደሚችል የግብርና ሚኒስቴር አስታወቀ።

የአንበጣ መንጋው 25 ዓመታት ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እስካሁን ያደረሰው ጉዳት የመጀመሪያ ግምታዊ ሥሌት እንደሆነ የገለጹት የግብርና ሚኒስትሩ አቶ ዑመር ሁሴን፣ ከመኸር ሰብል ምርት በተጨማሪ በእንስሳት መኖ ላይም ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰ አስረድተዋል።

በመጀመሪያ ዙር የአንበጣ መንጋው ጉዳት ያደረሰባቸው አካባቢዎች አማራ፣ አፋር፣ ኦሮሚያ፣ ትግራይ፣ ሶማሌ ክልሎችና የድሬዳዋ አስተዳደር እንደነበሩ የገለጹት ሚኒስትሩ፣ ለሁለተኛ ጊዜ ወረርሽኙ መከሰቱን ጠቁመዋል።

ከጥቂት ወራት በፊት በመጀመርያ ዙር ተከስቶ የነበረውን የአንበጣ መንጋ ወረርሽን ሙሉ ለሙሉ መቆጣጣር የተቻለ ቢሆንም፣ በሁለተኛ ዙር በሶማሌ ክልል ድንበር አካባቢ ሠፍሮ የነበረውናኬንያ በኩል በተለይም በደቡብ፣ኦሮሚያና በሶማሌ ክልሎች ውስጥሚገኙ 18 ዞኖች ተከስቷል ብለዋል።

በእነዚህ በተጠቁሱት ሥፍራዎች 195 ሺሕ ሔክታር የአንበጣ ወረርሽኝ  ያረፈበትን ሰብል ጨምሮ፣ 13 የርጭትና የዳሰሳ አውሮፕላኖች በመጠቀም 395 ሺሕ ሔክታር በላይ በአዝዕርትና በሰብል የተሸፈነ መሬት ላይ ኬሚካል መረጨቱን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ 2014 .ም. መጨረሻ ጀምሮ ወደ አገር ውስጥ የሚገባውን የስንዴ ምርት በማቆም፣ በአገር ውስጥ ምርት ለመሸፈን እየተሠራ ያለውን የአንበጣ መንጋ እንዳያስተጓጉል በከፍተኛ ሁኔታ እየተሠራ እንደሆነም ሚኒስትሩ አስረድተዋል።

የመስኖ ልማትን ለመደገፍ የሚያግዙ የግብርና ማሽነሪዎችን መንግሥት ከውጭ እያመጣ እንደሆነና በአገር ውስጥም ዘመናዊ ማሽነሪዎች ማምረት መጀመሩን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፣ 12 ሺሕ በላይ አርሶ አደሮች ስንዴማምረት ላይ መሰማራታቸውን ተናግረዋል።

በተያዘውመት 260 ሺሕ ሔክታር በላይ መሬት በሁለት ዙር ለማልማት ታቅዶ፣ 90 ሺሕ ሔክታር የሚጠጋ መሬት ስንዴ በመብቀል ላይ እንደሆነም አስታውቀዋል

ስንዴን በመስኖ ለማልማት በሚፈለገው መጠን አስፈላጊ የሆኑ መሣሪያዎችም እየቀረቡ እንደሆነና በተያዘው ዓመት አገሪቱ በየዓመቱ ከምታስገባው ወደ 20 ሚሊዮን ኩንታል የሚጠጋ ስንዴ ውስጥ፣ ግማሹን በአገር ውስጥ የማምረትቅድ ተይዞ እየተሠራ እንደሆነ ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች