Saturday, April 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊገቢዎች ሚኒስቴር ሁለት ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዙን አስታወቀ

ገቢዎች ሚኒስቴር ሁለት ቢሊዮን ብር ግምት ያላቸው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዙን አስታወቀ

ቀን:

በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያው ስድስት ወራት ውስጥ ከ1.9 ብር በላይ ግምታ ዋጋ ያላቸው የገቢና ወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች መያዛቸውን የገቢዎች ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴሩ እንደገለጸው፣ በስድስት ወራት ውስጥ ከተያዘው ኮንትሮባንድ ዕቃ 1,988,214,981 ብር ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ አንድ ቢሊዮን 608 ሚሊዮን 582 ሺሕ 897 ብር የሚገመቱ የገቢ ኮንትሮባንድ ዕቃዎችና ሕገወጥ ገንዘብ ነው፡፡ 379 ሚሊዮን 632 ሺህ 084 ብር የሚገመቱት ደግሞ  የኮንትሮባንድ ዕቃዎችና ከአገር ሊወጡ ሲል የተያዙ ሕገወጥ ገንዘብ መሆኑን ገልጿል፡፡

የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹ የተያዙት 14 ቅርንጫፍ ሕፈት ቤቶች ሲሆን፣ሐዋሳ፣ ጅግጅጋና ድሬዳዋ የሚገኙ ቅርንጫፍ ሕፈት ቤቶች ከፍተኛዋጋ ግምት ያላቸው የገቢ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ሥር እንዲውል በማድረግ ቀዳሚውን ሥፍራ ሲይዙ፣ የወጪ ኮንትሮባንድ ዕቃዎች ሞያሌ፣ አዲስ አበባ ኤርፖርትናሐዋሳ ከፍተኛ ዋጋ ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃዎች የያዙ መሆናቸውም ተጠቅሷል።

ከአገር ሊወጡ ሲሉ የተያዙት ኮንትሮባንድ ዕቃዎች አደንዛኝ ዕፆች፣ ሕገወጥ የገንዘብ ዝውውርና ማዕድናት ከአንድ እስከ ሦስት ያለውን ደረጃ ሲይዙ ወደ አገር በመግባት ላይ እያሉ የተደረሰባቸው ዋና ዋና የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ደግሞ ተሽከርካሪዎች፣ አዳዲስ አልባሳትና ኤሌክትሮኒክስ ናቸው፡፡

ሚኒስቴሩ የኮንትሮባንድ ዕቃዎቹን በመያዝ የተሳተፉ የጉምሩክ አመራርና ሠራተኞች እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የፀጥታ አካላትን አመስግኗል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...