Sunday, April 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስፈጻሚ ግብረሃይል አመራር ላይ ለውጥ ተደረገ

የትግራይ ክልል የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ አስፈጻሚ ግብረሃይል አመራር ላይ ለውጥ ተደረገ

ቀን:

በትግራይ ክልል የታወጀውን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ እንዲያስፈጽም የተቋቋመው ግብረሃይል የሚመሩት አዛዥ ተቀየሩ።

በትግራይ ክልል የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አስፈጻሚ ግብረሃይል በሀገር መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታማዦር እንዲመራና ተጠሪነቱ ለጠቅላይ ሚንስትሩ እንደሚሆን በአዋጁ የተደነገገ ሲሆን በዚሁ መሠረት እስከ ዛሬ የካቲት 24 ቀን 2013 ዓም በጄነራል ብርሃኑ ጁላ ሲመራ ቆይቷል። 

ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አህመድ የካቲት 24 ቀን 2013 ዓም ከትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደርና የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አስፈጻሚ ግብርሃይል ጋር ከተወያዩ በኋላ በግብረሃይሉ አመራር ላይ ለውጥ መደረጉን አስታውቀዋል። 

ይህንን ተከትሎ የጠቅላይ ሚንስትር ጽ/ቤት ቃል ከቀባይ አመሻሹን ባወጣው መግለጫም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አስፈጻሚ ግብረሃይል በጄነራል ዮሐንስ ገብረ መስቀል ተስፋ እንዲመራ መወሰኑን አስታውቋል። 

ከዚህም ባሻገር በትግራይ ክልል ሰብዓዊ ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ የተራድኦ ድርጅቶች ለሠላም ሚንስቴር ብቻ እያሳወቁ በክልሉ በየትኛውም ቦታ የሀገሪቱን ህጎች አክብረው በነፃነት እንዲንቀሳቀሱ የተወሰነ ሲሆን ፤ የተራድኦ ተቋማቱ በሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለሚደርስባቸው ማንኛውም አደጋ ኃላፊነቱን እራሳቸው እንደሚወስዱም አስታውቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኦቲዝምን ለመቋቋም በጥምረት የቆሙት ማዕከላት

ከኦቲዝም ጋር የሚወለዱ ልጆች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ...

አወዛጋቢው የወልቃይት ጉዳይ

የአማራና ትግራይ ክልሎችን እያወዛገበ ያለው የወልቃይት ጉዳይ ዳግም እየተነሳ...

ተጠባቂው የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የውድድር መለኪያ የሆነው የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በኢትዮጵያ

የሞባይል ገንዘብ ዝውውር የሞባይል ስልክን በመጠቀም ሊገኙ የሚችሉ የፋይናንስ...

የአማራና ደቡብ ክልሎች ለሠራተኛ ደመወዝ መክፈል መቸገራቸውን የፓርላማ አባላት ተናገሩ

በአማራና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት...