Monday, March 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊ‹‹ልብ ይበሉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥጋት መሆኑን ቀጥሏል›› የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

‹‹ልብ ይበሉ የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ሥጋት መሆኑን ቀጥሏል›› የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት

ቀን:

ኮቪድ-19 አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ በአገራችን ከዕለት ወደ ዕለት እየጨመረ ይገኛል፣ በቫይረሱ የሚያዙ፤ ሕይወታቸውን እያጡ ያሉ፤ ወደ ጽኑ ሕሙማን ክፍል እየገቡ የሚገኙ የኅብረተሰብ ክፍሎች ቁጥር እያሻቀበ ነው።

የካቲት 24 ቀን 2013 ዓ.ም. ለ6,282 ግለሰቦች የኮቪድ-19 የላቦራቶሪ ምርመራ የተደረገ ሲሆን፣ ከእነዚህም ውስጥ 1,161 ግለሰቦች በኮቪድ-19 ቫይረስ ተይዘዋል። ይህም ማለት ናሙና ከሰጡ 100 ግለሰቦች 18 ወይም (18%) ግለሰቦች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ያሳያል።

የኮቪድ-19 ወረርሽኝ መከላከያ መንገዶችን በአግባቡ አለመተግበራችን ዋጋ እያስከፈለን ይገኛል። በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ተይዘው ወደ ጽኑ ሕሙማን ክፍል የሚገቡ ግለሰቦች ቁጥርም እየጨመረ የሚገኝ ሲሆን፣ እስከ ረቡዕ ዕለት ብቻ 398 ግለሰቦች በጽኑ ሕሙማን ክፍል ውስጥ ይገኛሉ፤ ኮቪድ-19 ወደ ኢትዮጵያ ከገባ ዕለት ጀምሮ ይኼ ቁጥር ከፍተኛ ሆኖ ተመዝግቧል፡፡ ወደ ኮቪድ-19 የሕክምና ማዕከል ከሚገቡት 100 ግለሰቦች 69 የሚሆኑት በተለያየ መጠን ኦክስጅን የሚያስፈልጋቸው ሲሆን፣ የካቲት 25 ቀን በደረሰን መረጃ ብቻ 19 ያህል ግለሰቦች ሰው ሠራሽ የመተንፈሻ መሣሪያ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

አሁንም ልብ ይበሉ! በኢትዮጵያ በኮቪድ-19 ቫይረስ የሚያዙ ሰዎች ቁጥር  ወደ ጽኑ ሕሙማን ክፍል የሚገቡ ሰዎች ቁጥር፣ እንዲሁም በኮቪድ-19 ሕይወታቸውን የሚያጡ ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ ስለመጣ እያንዳንዱ ግለሰብ፣ ቤተሰብ መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች፣ የሃይማኖት ተቋማት፣ ሲቪክ ማኅበራትአገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የጤና ባለሙያዎች፣  መምህራንና ሌሎችም ባለድርሻ አካላት ማስክ ማድረግ፣ የእጃቸውን ንፅህና በተደጋጋሚ መጠበቅና በየትኛውም ቦታ አካላዊ ርቀትን በመጠበቅ ተገቢውን የጥንቃቄ መንገዶችን በመተግበር ራስዎንም እንዲሁም ወገንዎን ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ እንዲጠብቁ የኢትዮጵያ የኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት በአጽንኦት ያሳስባል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...