Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልየጣይቱ ባህልና ትምህርት ማዕከል የአዲስ አበባን ጥንታዊ ሕንፃ ተረከበ

የጣይቱ ባህልና ትምህርት ማዕከል የአዲስ አበባን ጥንታዊ ሕንፃ ተረከበ

ቀን:

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የፌደራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት የአራዳ ምድብ ችሎት ይጠቀምበት የነበረውን የቢትወደድ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል መኖሪያ ቤትን ለጣይቱ ባህልና ትምህርት ማዕከል አስረከበ። 

ጣይቱ የባህልና ትምህርት ማዕከል፣ በአንጋፋዋ ከያኒት ዓለም ፀሐይ ወዳጆ ከሁለት አሠርታት በፊት በአሜሪካ ተቋቁሞ በኪነ ጥበብ ላይ ሲሠራ የነበረ ነው፡፡ 

በቅርስነት የተመዘገበው ነባር ሕንፃ ለጣይቱ ባህልና ትምህርት ማዕከል ያስረከቡት የአዲስ አበባ ምክትል ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ፣ በሥነ ሥርዓቱ ላይ እንደተናገሩት፣ የትናንቱ ትውልድ ያስቀመጣቸውን መልካም አሻራዎች እንዳይደበዝዙ፣ ከነጥንታዊነታቸው፣ ከነታሪካቸውና ከነፋይዳቸው ለተተኪው ትውልድ ለማስተላለፍ በአግባቡ መጠበቅና መንከባከብ ይገባል፡፡ 

 የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መካነ ቅርሱን ለማደሻ የሁለት ሚሊዮን ብር ድጋፍ ማድረጉን የከተማ አስተዳደሩ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያሠራጨው መረጃ ያመለክታል፡፡ 

በሥነ ሥርዓቱ ላይ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትርና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኰንን፣ ሚኒስትሮችና የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች ተገኝተዋል፡፡ 

የቢትወደድ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል መኖሪያ ቤት ከ117 ዓመታት በፊት መገንባቱ ይታወቃል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...