Friday, March 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ኪንና ባህልኮቪድ-19 ያስተጓጐለው 7ኛው የጉማ ሽልማት መጋቢት 18 ሊካሄድ ነው

ኮቪድ-19 ያስተጓጐለው 7ኛው የጉማ ሽልማት መጋቢት 18 ሊካሄድ ነው

ቀን:

በኮቪድ -19 ወረርሽኝ ምክንያት ዓምና ያልተካሄደው ጉማ የፊልም ሽልማት፣  መጋቢት 18 ቀን 2013 .ም. በስካይላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ታወቀ፡፡

አዘጋጆቹ በስካይላይት ሆቴል በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እንደገለጹት፣ ለሰባተኛ ጊዜ የሚካሄደው የጉማ ፊልም ሽልማት 2011 እና 2012 ዓ.ም. ተሠርተው በአገር ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ ለእይታ ከቀረቡ ፊልሞች መካከል 45ቱ ለውድድር ተመዝግበዋል፡፡ በተደረገው ማጣራት 18 ምድቦች ለፍጻሜው ውድድር የሚቀርቡ ፊልሞች ነገ (ሐሙስ) ይፋ እንደሚደረጉም ገልጸዋል፡፡

የዘንድሮው የሕይወት ዘመን ተሸላሚ በመሆን የተመረጡት አንጋፋው ጸሐፌ ተውኔት፣ ገጣሚና የዜማ ደራሲ የፊልም ተዋናይ ተስፋዬ አበበ (ፋዘር) ናቸው፡፡

ሃቻምና በተካሄደው የጉማ ፊልም ሽልማት ስመ ጥሩ የፊልም ባለሙያ ኃይሌ ገሪማ (ፕሮፌሰር) የሕይወት ዘመን ተሸላሚ ሆነው መመረጣቸው ይታወሳል፡፡ ያለ ተወዳዳሪ የሕይወት ዘመን ተሸላሚ የሆኑት ኃይሌ ገሪማ  ከሠሯቸው  ፊልሞች  መካከል  ቡሽ ማማ፣ ምርት ሦስት ሺሕ ዓመት፣ ሳንኮፋ፣ ዓድዋና ጤዛ ይገኙባቸዋል፡፡

የፊልም ሽልማቱ መጠርያውን ያገኘው ከአምስት አሠርታት ግድም በፊት በሚሼል ፓፓታኪስ ከተሠራው ‹‹ጉማ›› ከተሰኘ ፊልም መሆኑ ይታወቃል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...