Monday, March 27, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንታዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫን እሑድ ሊያደርግ ነው

ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንታዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫን እሑድ ሊያደርግ ነው

ቀን:

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ የፕሬዚዳንታዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ምርጫ እሑድ መጋቢት 19 ቀን 2013 ዓ.ም. በባህር ዳር ከተማ እንደሚያከናውን ገለጸ፡፡

የኦሊምፒክ ኮሚቴው መተዳደሪያ ደንብ በየአራት ዓመት አንድ ጊዜ ፕሬዚዳንታዊና የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን ምርጫ ማድረግ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ ይሁንና ከአንድ ዓመት በፊት የቻይና ግዛት በሆነችው ውሃን ከተማ በተከሰተው የኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ትልልቅ ዓለም አቀፍ ጉባዔዎችን ጨምሮ በርካታ ፕሮግራሞች እንዲሸጋሸጉ ተደርገው ቆይተዋል፡፡ ከእነዚህ ፕሮግራሞች መካከል ባለፈው ዓመት መካሄድ የነበረበት የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ምርጫ ይጠቀሳል፡፡

የምርጫ አስፈጻሚ ኮሚቴው፣ ለቀጣዩ አራት ዓመታት ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴን ለመምራት ለፕሬዚዳንትነትና ለሥራ አስፈጻሚነት ዕጩ ሆነው የቀረቡ 21 ብሔራዊ ፌዴሬሽኖችንና አሶሴሽኖችን ባለፈው ሳምንት ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡

ኦሊምፒክ ኮሚቴው የካቲት 19 ቀን 2013 ዓ.ም. በቢሾፍቱ አዱላላ ሆቴል ባካሄደው አስቸኳይ ጉባዔ፣ የምርጫ ማስፈጸሚያ መመርያና ሦስት ኮሚቴ ያለው የምርጫ አስፈጻሚ አባላትን መሰየሙ ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...