Friday, September 29, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ሊዝ ፋይናንሲንግ ከ18 ወራት በኋላ ሊጀምር መሆኑ ተገለጸ

ተዛማጅ ፅሁፎች

አስገዳጅ የነበረው 20 በመቶ መዋጮ ይቀራል ተብሏል

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ይሰጥ የነበረው የሊዝ ናንሲንግ አገልግሎት ከቆመ 18 ወራት በኋላ ሊጀመር መሆኑንና በብድር ለሚያቀርባቸው ማሽኖችና የካፒታል ዕቃዎች ተጠቃሚዎች በቅድሚያ የ20 ከመቶ የመዋጮ ክፍያ እንዲከፍሉ የሚያስገድደውን የመመያ ድንጋጌ ለማስቀረት አዲስ መመያ እያዘጋጀ መሆኑን የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አስታወ፡፡

አዲ መመግጅት የተገለጸው ባለፈው መጋቢት 22 ቀን 2013 ዓ.ም. ሲሆንዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግት ወጪ አስተዳደርና ቁጥጥር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ጠሪነት በተካሄደው ይፋዊ ዝባዊ ስብሰባ ላይ ነው፡፡

በስብሰባው ላይ የተገኙት የባንኩ የሥራ ኃላፊዎች በኦዲት ወቅት የተከለሱ ማስረጃዎችንና የናሙና ጥናቶችን መረት በማድረግ ተዘጋጅቶ በቀረበው የኦዲት ሪፖርት መነሻነት ከቋሚ ኮሚቴው ለቀረቡ ጥያቄዎች ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ልማት ባንክ ከ2009 በጀት ዓመት አስከ 2012 የመጀመያው ሩብ ዓመት ድረስ ለአነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ባቀረበው የካፒታል ዕቃዎች ኪራይ የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ውጤታማነት ላይ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ያካሄደውን የክዋኔ ኦዲት ሪፖርት መሠረት የተደረገ ውይይት ነበር፡፡

የዋና ኦዲተር መሥሪያ ባቀረበው ሪፖርት ውስ በተካተቱ የኦዲት ግኝቶችንና በተጠቆሙት የማሻሻያ ምክረ ሳቦች መንተራስ በቋሚ ኮሚቴውና በአባቱ በተናርካታ ጥያቄች ለባንኩ ኃላፊዎች ቀርበዋል፡፡ ከቀረቡት ዋነኛ ጥያቄዎች ውስጥ በአገሪቱ ሙያና ችሎታ ኖሯቸው ከመደበኛ ባንክ መበደር ማይችሉ ወይም የባክ ማስያዣ (ኮላተራል) ማቅረብ ለማይችሉ ኢንተርፕራዞች የካፒታል ዕዎችን በሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ታስቦ የተጀመረ ፕሮግራም ሆኖ ሳለ አገልግሎቶ ከጥቂት ጊዜ በኋላ በኞች 20 መቶ መዋጮ ከግ አግባብ ውጪ በሰርኩላር አስገዳጅ ድንጋጌ በመተግበር በደንበኞች ላይ ቅራኔ መፍጠሩን እንዲሁም መዋጮ መጠየቁ ከሊዝ ፋይናንሲንግ ፖሊሲና የአራር ፕሮሲጀር ስለመቃረኑ ጥያቄዎች ቀርበዋል፡፡

ከቋሚ ኮሚቴው ለተነሳላቸው ጥያቄዎች ምላ የሰጡት የልማት ባን ፕሬዚዳንት ዮንስ አያሌው (ዶ/ር) የ20 በመቶ አስገዳጅ መዋጮን በተመለከተ በዋና ኦዲተር ትም ሆ በቋሚ ኮሚቴ አባላት የመነሳቱን ተገቢነት ተናግረዋል፡፡ የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎቱ በጀመረበት ወቅትራ ላይ ነበረው የመጀመያ መመያ ተጠቃሚዎች መዋጮ የማይጠይቅ እንደነበር፣ ደንበኞች የዕዳ ክፍያና ብድርን በጊዜ ለመክፈል ፍላጎት ካለማሳየተቸው ጋር ተያይዞ ባንኩ ጋጠሙትን በርካታ ችግሮች ለመፍታት ታስቦ  መመያውን ለማሻሻል መገደዱን አስረድተዋል፡

‹‹ነገር ግን አሁን ይህንን መመያ በመከለስ ቀድሞ በነበረው የአራር መመያ መረት አዲስ መመያ እያዘጋጀን ነው፡፡ በመሆኑም ደበኞች ከዚህ በኋላ በሊዝ ፊይናንሲወስዱት ወይም ለሚከራዩት ምንም ይነት መዋጮ አይከፍሉም፤›› ብለዋል፡፡ ባንኩ ቀደም ሲል ባገጠሙት ዘርፈ ብዙ ችግሮችና በተለያ ምክንያቶች ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት አቋርጦት የነበረውን የሊዝ ፋይናንሲንግ ኪራይና ብድር በቅርቡ መስጠት እንደሚጀምረም ፕሬዚዳንቱ ለቋሚ ኮሚቴው አስረድተዋል፡፡

አገልግሎቱ ሲጀምር በሊዝ ፋይናሲንግ ለደንበኞች ባንኩ ከውጭ ገበያ የሚያስገባቸውን ማሽኖ 80 በመቶ ወጪ የሚሸፈን ሆኖበኞች 20 መቶ የሚሆን የራ ማኬጃ ካፒታል ማስመዘገብ ቻ እንደሚጠበቅባቸው ፕሬዚዳንቱ አስረድተዋል፡፡ አክለውም ባንኩ ቀደም ሲል በነበረበት ብልሹ አሠራር በርካታ ችግሮች የነበሩበት በመሆኑ ከሪፎርሙ በኋላ በአዲስ አመራርና ቦርድ ችግሮቹን ለመቅረፍ የሚያስችሉ ርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ቋሚ ኮሚቴ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ያሉበትን የኦዲት ግኝቶች በገመገመበት ወቅት ባንኩ ከደት ባለፈ ተጨባጭ አመርቂ ውጤቶችን እያስመዘገበ አለመሆኑን በመተቸትራሩ በአዳዲስ ዘዴዎች በመደገፍ የተለ የራ ክንዋኔ መተግበር የሚያስችል ዘዴዎችን እንዘረጋና ከፍተቶችን በፍጥነት ማሻሻል እንዳለበት አሳስቧል፡፡

የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት አዲስ አሠራር እንደመሆኑ በተገልጋይ ኢንተርፕራይዞች እንዲሁም በባለድርሻ አካላትና በባንኩ ሠራተኞች ጭምር ስለአራሩ በቂ ግንዛቤ ያለመኖሩ፣ በቅንጅት አሠራር ክፍተት ምክንያት አገልግሎቱን ሊያገኙ የሚገባቸው ዕውቀትና ክህሎት ያላቸው ኢንተርፕራይዞችን በመመልመል ደት ችግር መኖሩና ወጥ የሆነ የአሠራር ፖሊሲ ባለመኖሩ በተገልጋዮች ዘንድ ቅሬታ መፈጠሩ በቋሚ ኮሚቴው ተገልጿል፡፡

የካፒታል ዕቃዎች ለኢንተርፕራይዞቹ ከመቅረባቸው በፊት በሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊ የሆኑ መረተ ልማቶች መዘጋጀታቸውን የማረጋገጥ ክፍተት መኖሩ፣ ከሚቀርቡት ማሽነሪዎች ውስጥ በዓይነት ያልተለዩና መፈርት የሌላቸው ውስብስብ፣ ትልልቅና ለመትከል አስቸጋሪ የሆኑ በመኖራቸው በተለያዩ ምክንያቶች ማሽነሪዎቹን ለስተኛ ወገን ማስተላለፍ ቢፈለግ ከቦታ ቦታ በቀላሉ ማንቀሳቀስ የማይቻል መሆኑ ቋሚ ኮሚቴው ባቀረባቸው ጥያቄዎች እንደ ክፍተት ተነስተዋል፡፡

በተጨማሪም ለኢንተርፕራይዞች የሚቀርቡ የካፒታል ዕቃዎች ምዝገባ በሚመለከታቸው አካላት ስም በአግባቡ ሳይመዘገቡ ለተከራዮች የሚተላለፉ መሆኑ፣ ከውጭ ለሚገቡ ዕቃዎች አስፈላጊውን የጉምሩክ ሰነድ በቅድሚያ ያለማዘጋጀትና ዕቃዎችን በወቅቱ ከወደብ የማንሳት ችግር በመኖሩ ተገልጋዮች ለተጨማሪ ወጪና እንግልት መዳረጋቸው፣ እንዲሁ ዋና ብድርና የወለድ ክፍያዎች በወቅቱ ያለመሰብሰብ ችግሮች በባንኩ ላይ የተነሱ ጥያቄዎች ናቸው፡፡

በተጨማሪ ባንኩ የግዥ መመያ የሌለው መሆኑን፣ የግ መመያን ያልተከተሉ ግዥዎች መፈጸማቸውና የመድን ዋስትና ያልተገባላቸው ዕቃዎች መኖራቸው እንዲሁም ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የመራት የጎላ ክፍተት መኖሩን የኦዲት ግኝቱ እንደሚያሳይ በቀረቡት ጥያቄዎች አማካይነት ተጠቅሷል፡፡

የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራው ክፍተት የነበረበት መሆኑን የጠቆሙት ዮንስ (ዶ/ር)፣ በአሁኑ ወቅት ክልሎችን ጨምሮ ለተለያዩ ባለድርሻ አካላትና ለተገልጋዮች እንዲሁም ለባንኩ ተኞች ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጥ ተግባር እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ከተለያዩ የገሪቱ ክፍሎች ለተውጣጡ 2,500 አዳዲስና ነባር ኢንተርፕራይዞች በአደረጃጀት፣ በፋይናንስ፣ በአስተዳደርና በሌሎች ተዛማጅ የባንኩ አሠራሮች ላይ ልጠናዎች እየተሰጡ መሆናቸውን በማሳያነት የጠቀሱት ፕሬዚዳንቱ ኢንተርፕራይዞች የባንኩን አገልግሎት የሚያገኙት በአነስተኛ ወለድና ከማሽነሪያቸው ውጪ ሌላ ማስያዣና ዋስትና ሳይፈለጋቸው መሆኑንም ግንዛቤ እየተሰጠ እንደሚገኝ ጨምረው አብራርተዋል፡፡    

ቀደም ሲል በነበረው የባንኩ አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ወጥ የሆነ አሠራር ያልነበረና የባንኩ ራተኞችም ጭምር የተሳተፉባቸው የተንዛዙና ብልሹ አራሮች የእንደነበሩ የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ ከብልሹ አራሮች ጋር ግንኙነት በነበራቸው ራተኞች ላይ ርምጃ መወሰዱን ገልጸዋል፡፡ አክለውም በተንዛዛ በብልሹ አሠራርና በግንዛቤ ጉድለት ምክንያት ዋና ብድርና ወለድን በወቅቱ ያለመሰብሰብ ችግር በባንኩ አሠራር ላይ ሲታይ የነበረ መሆኑን በመጥቀስ ይህንንም ችግር ለመቅረፍ በተካሄደው የሪፎርምና የግንዛቤ ማስጨበጥ እንዲሁም በተደረገው ከፍተኛ ጥረት ባለፉት ጥቂት ወራት ብቻ ከ1.2 ቢሊዮን ብር በላይ መሰሰቡን በዋነት አንስተው የተበላሸ የብድር መጠንም በፊት ከነበረበት ዝቅ እንዲል መደረጉን ጠቁመዋል፡፡ 

በተለያዩ የባንኩ አሠራሮች ላይ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት የመራት ደቱን ለማሻሻል ከክልሎችም ሆነ ከከተማ መስተዳሮች እንዲሁም ሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር ለመራት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ዮሐንስ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡

የኦዲት ሪፖርቱን መረት በማድረግ የድርጊት መር ግብር ተዘጋጅቶ ለፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት ያለ መላኩ የተወሰዱ የማስተካከያ ርምጃዎች ሪፖርት ያለ መደረጋቸው ክፍተት በመሆናቸው ወደፊት የሚስተካከሉ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው የክዋኔ ኦዲት ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወ/ሮ ወይንሸት ገለሶ በበኩላቸው ባንኩ የነበሩበትን ችግሮች በሪፎርም ውስጥ አካቶ ለመቅረፍ ጥረት እያደረገ ቢሆንም ለፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በወቅቱ መላክ የነበረባቸው የድርጊት መር ግብርና የማስተካከያ ርምጃ ሪፖርቶች ያለ መላካቸው በመተቸት ወደፊት መስተካከል የሚገባው ነው ብለዋል፡፡ ባንኩ እያከናወነ ያለው የሪፎርም ራ ፈጣን ለውጥ ሊያመጣ የሚችል መሆን እንደሚገባው ወ/ሮ ወይንሸት  አሳስበዋል፡፡

የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት የኦዲት ዘርፍ ምክትል ዋና ኦዲተር ወ/ሮ መሠረት ዳምጤባንኩ የሪፎርም እንቅስቃሴና ለለውጥ ያለው ፍላጎት አበረታች መሆኑን ቢገልጹም የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት በገሪቱ አዲስ አራር እንደ መሆኑና የታዩት አብዛኞቹ ክፍተቶችም ከግንዛቤና ከሌሎች አካላት ጋር ተቀናጅቶ ባለመራት የተፈጠሩ መሆናቸው አመልክተዋል፡፡ ይሁን እንጂ በአሠራሩ ላይ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫና ተቀናጅቶ የመራት ራዎች ተጠናክረው መቀጠል እንደሚኖርባቸው አሳስበዋል፡፡

የባንኩ የክትትልና የቁጥጥር ሥራ በሚፈለገው ደረጃ ላይ ያለመሆኑን የኦዲት ግኝቱ የሚያሳይ መሆኑን የገለጹት ምክትል ዋና ኦዲተሯ ኢንተርፕራይዞችን ከአነስተኛ ወደ መካከለኛ ለማሸጋገርና ባንኩን ወጥ በሆነ ፖሊሲና የአሠራር መመያ ለመምራት ያለው ዝግጁነት የበለጠ መጠናከር እንደሚኖርበት ጠቁመዋል፡፡

በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ መሐመድ የሱፍ ባንኩ ያሉበትን ችግሮች ለማስተካከል ጥረት እያደረገ መሆኑን በቀረበው ማብራሪያና ምላሽ ለመረዳት የተቻለ መሆኑን ጠቅሰው ችግሮቹን በዳሰሳ ጥናት በማስደገፍ ለመቅረፍ ቀጣይ ጥረቶች ማድረግ እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡

የባንኩን ዓላማ ለማሳካትም በተለይ ከክልሎች ጋር ያለውን አሠራር የበለጠ ማጠናከር እንደሚገባ በሳሰብ የተለያዩ ተሞክሮዎችን በመውሰድ ከገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ጋር በማሳለጥ የባንኩን የሊዝ ፋይናንሲንግ አገልግሎት ማጠናከር እንደሚገባ አመልክተዋል፡፡ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መሥሪያ ቤት በየጊዜው የሚሰጠውን አስተያየት በግብትነት በመውሰድ የባንኩን አሠራር ማጎልበት እንደሚገባ ሰብሳቢው በማጠቃለያ ንግግራቸው አሳስበዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች