Sunday, September 24, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ በ300 ሚሊዮን ዶላር የሚገነባውን የሕክምና ማዕከል የመሠረት...

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ በ300 ሚሊዮን ዶላር የሚገነባውን የሕክምና ማዕከል የመሠረት ድንጋይ አስቀመጡ

ቀን:

ወደ ውጭ የሚጓዙ ዜጎችን ያስቀራል የተባለውንና ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ ወጪ ይገነባል የተባለውን ሮሃ ሕክምና ማዕከል  ግንባታ የመሠረት ድንጋ ተቀመጠ። የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ /ር) ናቸው።
ከኢትዮጵያ  ወደ ውጭ አገሮች የሚጓዙ ዜጎችን ያስቀራል የተባለው    “የህክምና ማዕከል ሮሀ የህክምና ማዕከል” የሚል ስያሜ የተሰጠው ሲሆን ሙሉ ወጪውን ችሎ የሚገነባው ሮሃ ግሩፕ የተባለ የአሜሪካ ኩባንያ መሆኑንም፣ ዛሬ ሚያዝያ 2 ቀን  2013 ዓ.ም የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ ተነግሯል።
ግንባታው በአምስት አመታት ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሏል። የሕክምና ማዕከሉ የልብ ቀዶ ጥገና፡ የካንሰርና ዘርፈ ብዙ የሕክምና  አገልግሎት ይሰጣል ተብሏል፡፡ለ7,500  ዜጎች የስራ ዕድል  ከመፍጠሩም በተጨማሪ የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር ማዕከልም እንደሚሆንም የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ዮሀንስ ተናግረዋል ፡፡
 በየሕክምና ማዕከሉ ተኝተው ለሚታከሙ 1500 አልጋ ፡እንደሚኖረው ተገልጿል፡፡ ማዕከሉ የሚገነባው በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 13 ሀያት ሆስፒታል አካባቢ አድዋ ፓርክ ሜዳ ላይ ነው።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...