- Advertisement -

ለካፍ አካዴሚ ግንባታ የተፈቀደው ቦታ በፍርድ ቤት ታግዶ አርሶ አደሮች እንዲገብሩበት ተደረገ

ከካፍ የተረከበው ስፖርት ኮሚሽን ማብራሪያ አለመጠየቁን ገልጿል

የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን (ካፍ) 13 ዓመታት በፊት በአዲስ አበባ አያት አካባቢ ላስገነባው የምሥራቅናመካከለኛው አፍሪካ አገሮች ታዳጊ ወጣቶች የእግር ኳስ አካዴሚ ማስፋፊያ የተፈቀደው ቦታ፣ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መታገዱን የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን አስታወቀ፡፡ የአካባቢው አርሶ አደሮች 13 ዓመታት በኋላ እንደ አዲስ ግብር እንዲገብሩበት ስለመደረጉ ጭምር ተነግሯል፡፡

2000 .. ለአካዴሚው ማስፋፊያ እንዲሆን ቀድሞ በነበረው 30 ሺሕ ካሬ ሜትር ቦታ በተጨማሪ 20 ሺሕ ካሬ ሜትር በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ተሰጥቶ የነበረ ቢሆንም፣ ለማስፋፊያ በተሰጠው ቦታ ላይ በተነሳ ክርክር ከሥፍራው የተነሱ አርሶ አደሮች ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ነው ፍርድ ቤት ዕግዱን ያወጣው፡፡ ለማስፋፊያው ተጨማሪ የተሰጠው መሬት ላይ ለዓመታት ተቋርጦ የነበረውን ግብር ከዚሁ ዓመት ጀምሮ አርሶ አደሮቹ እንዲገብሩመደረጉ፣ ፍርድ ቤቱ ዕግዱን እንዲጥል መነሻ እንደሆነው ፌዴሬሽኑ አስታውቋል፡፡

እንደ ፌዴሬሽኑ ከሆነ ገበሬዎች 13 ዓመታት በኋላ ግብር እንዲከፍሉ ከተደረገ በኋላ ወደ ፍርድ ቤት ሄደው አቤቱታ አቅርበው የዕገዳ ውሳኔ ከመተላለፉ በፊት፣ የአካዴሚውን ካርታና የሳይት ፕላን ከካፍ የተረከበው ስፖርት ኮሚሽን፣ በጉዳዩ ማብራሪያ እንዲሰጥ አልተደረገም፡፡ በዚያ ላይ ኮሚሽኑ አካዴሚውን ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ለማስረከብ በሒደት ላይ ባለበት በዚህ ወቅት እንዲታገድ መደረጉ አግባብ እንዳልሆነ ጭምር፣ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ኢሳያስ ጅራ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡       

ካፍ በአዲስ አበባ የገነባው አካዴሚ የምሥራቅ አፍሪካ ታዳጊዎች የእግር ኳስ ልህቀት ማዕከል እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ሲሆን፣ ማስፋፊያውም ይኼንን ተግባር በስፋት ለማከናወን ያስችላል ተብሎ የተወሰነ ነበር፡፡
ብሔራዊ ፌዴሬሽኑ በታገደው ቦታ ላይ አንድ የተፈጥሮ ሳርና ሁለተኛውን ደግሞ በሰው ሠራሽ ሳር ሁለት ሜዳዎችን ለማስገንባት ስፖንሰር ተገኝቶ ተቋራጮችን ለማወዳደር በዝግጅት ላይ እንደነበርም ፕሬዚዳንቱ አክለዋል፡፡

አካዴሚውን ያስገነባው ካፍ ከሁለት ዓመት በፊት ቀድሞ የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ለነበሩት አቶ ርስቱ ይርዳው የአካዴሚውን ሙሉ ሰነድ እንዳስረከበ  ያስረዱት አቶ ኢሳያስ፣ ፌዴሬሽኑ ሁለቱን ሜዳዎች ማስገንባት ይችል ዘንድ ከሁለት ወራት በፊት የመሬት መጥረጊያ ማሽኖችን በማስገባት ዋናውን ሥራ ጀምሮ ነበር፡፡

- Advertisement -

ችግሩን ተከትሎ ከወር በፊት ከተመረጡት የካፍ አመራሮች መካከል ከጽሕፈት ቤት ኃላፊውና ከፕሬዚዳንቱ ጋር መነጋገራቸውን ያስረዱት አቶ ኢሳያስ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት ይህን ጉዳይ በጥሞና ተመልክተው አፋጣኝ የመፍትሔ አቅጣጫ ሊያበጁለት እንደሚገባ ጠይቀዋል፡፡
አካዴሚው ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ የተለያዩ ቢሮዎችና የስብሰባ አዳራሾች፣ ስፖርተኞች የሚተኙባቸው 42 ክፍሎችና የላውንደሪ ማሽኖች፣ እንዲሁም አንድ ዓለም አቀፍ አካዴሚ ሊያሟላቸው የሚገቡ ጅምናዚየሞችን አሟልቶ የያዘ በመሆኑ፣ ለብሔራዊ ቡድኖች ዝግጅት አገልግሎት መስጠት ከጀመረም ሰነባብቷል፡፡

የዓለም አቀፍ እግር ኳስ ማኅበር (ፊፋ) ከዓመት በፊት በአዲስ አበባ የከፈተውን ቀጣናዊ ጽሕፈት ቤት ምክንያቱን ሳያሳውቅ ወደ ሩዋንዳ ማዛወሩ ይታወሳል፡፡

- Advertisement -

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን

ከ ተመሳሳይ አምዶች

ለከተራና ጥምቀት በዓላት ትኩረት የሚሹት ለኮሪደር ልማት የተቆፋፈሩ መንገዶች

የዘንድሮ የጥምቀት በዓል በተለይ በአዲስ አበባ ለየት ባለ ጥበቃ የሚከበር ስለመሆኑ የአዲስ አበባ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ አስታውቋል፡፡ የደንብ ማስከበር ባለሥልጣንና ሌሎች አካላትም በዓሉ በሰላም...

ኢትዮጵያዊቷ ተማሪ የ2025 የሁዋዌ ዓለም አቀፍ አምባሳደር ሆና ተመረጠች

የሥላሴ ዩኒቨርሲቲ አራተኛ ዓመት የኮምፒዩተር ሳይንስ ተማሪ አሲያ ከሊፋ የሁዋዌ የ2025 የሲድስ ፎር ዘ ፊውቸር ዓለም አቀፍ አምባሳደሮች አንዷ ሆና ተመረጠች፡፡ ሁዋዌ ከመረጣቸው 12 አምባሳደሮች...

የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀዬአችን እንድንመለስ ድምፅ ይሁነን ሲሉ ጠየቁ

ከሰኞ ጥር 5 ቀን 2017 ዓ.ም. ጀምሮ ለሦስት ቀናት የተቃውሞ ሠልፍ በመቀሌ ከተማ እያካሄዱ ያሉት የትግራይ ክልል ተፈናቃዮች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምፅ እንዲሆናቸው ጠየቁ፡፡ በፕሪቶሪያ...

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በታጣቂዎችና ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰዎች ሕይወት ማለፉ ተገለጸ

በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በመተክል ዞን ቡለን ከተማ፣ በሸኔ ታጣቂዎችና በክልሉ ሚሊሻዎች መካከል በተከፈተ ተኩስ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ተሰማ፡፡ የክልሉ ነዋሪዎች ‹‹የሸኔ ኃይሎች›› በማለት ወደ የጠሯቸው...

መንግሥትና ታጣቂዎች በየትኛውም ቦታና ሰዓት ለመነጋገር ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ ዝግጁ መሆኗን አሜሪካ አስታወቀች

የሲቪክ ምኅዳሩ ሊጠበቅና ሚዲያዎች በነፃነት ሊሠሩ ይገባል ተብሏል ‹‹በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች መንግሥትና ታጣቂዎች ገንቢ በሆነ መንገድ በየትኛውም ቦታና ጊዜ ሰላማዊ ንግግር ለማድረግ ዝግጁ ሲሆኑ ለማገዝ...

መንግሥት ባለፉት አምስት ዓመታት 1.5 ሚሊዮን ቤቶችን ገንብቻለሁ አለ

የንብረት ታክስ አዋጅ እምብዛም ማስተካከያ ሳይደረግበት መፅደቁ ቅሬታ ፈጥሯል መንግሥት ኢሕአዴግ መንግሥት ሆኖ አገሪቷን ሲያስተዳድር ለ14 ዓመታት (ከ1996 እስከ 2010 ዓ.ም.) በአገሪቱ ከገነባቸው ኮንዶሚኒየም የጋራ...

አዳዲስ ጽሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ቀኑን ሙሉ ከዋሉበት የሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ተመልሰው ከባለቤታቸው ጋር እያወጉ ነው]

የምን ስብሰባ ላይ ዋልኩ ነበር ያልከኝ? የሥራ አስፈጻሚ። የምን ሥራ አስፈጻሚ? የገዥው ሥራ አስፈጻሚ። ምን ገጥሟችሁ ነው የተሰበሰባችሁት? ለመረጠን ሕዝብ ቃል የገባናቸውን ተግባራት አፈጻጸም የምንገመግምበት የተለመደ ስብሰባ ነው። የገባችሁት ቃል...

ሕወሓትን አጣብቂኝ ውስጥ የከተተው መመርያ

በሁለት አንጃ ተከፍሎ የእርስ በርስ የቃላት ጦርነት ውስጥ የገባው ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ (ሕወሓት) ልዩነቱን ትቶ ወደቀድሞው አንድነቱ በመመለስ የሚጠበቅበትን ጠቅላላ ጉባዔ የማድረግ አልያም...

ባንኮች እየፈጸሙት ያለው አቅርቦትንና ፍላጎትን ያላገናዘበ የውጭ ምንዛሪ ግዥ

የውጭ ምንዛሪ ግብይት በገበያ ዋጋ እንዲገበይ የወጣው ሕግ ተግባራዊ መሆን ከጀመረ ከሰባት ወራት በላይ አስቆጥሯል፡፡ ሕጉ ተግባራዊ በተደረገበት የመጀመርያው ቀን የአንድ ዶላር የምንዛሪ ዋጋ...

አሳረኛው ኑሮ!

የዛሬው ጉዞ ከቦሌ ወደ ፒያሳ ይሆን ዘንድ ግድ ሆኗል፡፡ ለምን? በኑሮ  ምክንያት፡፡ የታክሲ መሠለፊያው ወሬ የነዳጅ ጭማሪውን ተከትሎ ስለሚመጣው ተጨማሪ ታሪፍ ነው፡፡ ‹‹የእኛ ኑሮ...

የግለሰቦች ለመብታቸው ኃላፊነት አለመውሰድ ለአገር ያለው አደጋ

በያሬድ ኃይለመስቀል አንድ የማከብረው ኢኮኖሚስት አንድ መጽሐፍ እንዳነብ መራኝና ማንበብ ጀመርኩኝ። ይህንን መጽሐፍ ሳነበው ከዋናው ሐሳብ ወጣ ብሎ ስለ “የነፃ ተጓዦች ሀተታ” (The Free Rider...

‹‹የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበራትን ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ ማጠናከር ያስፈልጋል›› አቶ ፍፁም አብርሃ፣ የአሚጎስ ብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር መሥራችና ሥራ አስኪያጅ

አሚጎስ የብድርና ቁጠባ ኅብረት ሥራ ማኅበር ከተመሠረተ አሥራ ሁለት ዓመታት ሆኖታል፡፡ በእነዚህ ዓመታት 8,500 አባላትን ማፍራት ችሏል፡፡ አሚጎስ ስለተመሠረተበት ዓላማ፣ እያከናወናቸው ስለሚገኙ ተግባራት፣ የብድርና...
[the_ad id="124766"]

በማህበራዊ ሚዲያዎች ይከታተሉን