Friday, March 31, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየሐረሪ ክልል ምርጫ ቦርድ ያስተላለፈበት ውሳኔ የክልሉን ሕገ መንግሥት ያላማከለና አመክንዮ የሌለው...

የሐረሪ ክልል ምርጫ ቦርድ ያስተላለፈበት ውሳኔ የክልሉን ሕገ መንግሥት ያላማከለና አመክንዮ የሌለው ነው አለ

ቀን:

የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚያዚያ 1 ቀን 2013 .ም. የሐረሪ ክልል ብሔራዊ ጉባዔን አስመልክቶ ያስተላለፈው ውሳኔ፣ የክልሉን ሕገ መንግሥት ያላማከለና ሕገ መንግሥትዊ አመክንዮ የሌለው ነው አለ፡፡

ከክልሉ ውጪ የሚኖረው የሐረሪ ክልል ከሕዝብ ባለፉት አምስት ምርጫዎች የመምረጥ መብት ተሰጥቶት የመረጠ ቢሆንም፣ ግንቦት 28 ቀን 2013 .. በሚካሄደው ምርጫ ላይ መሳተፍ የሚችለው በክልሉ በመገኘት እንጂ ከክልሉ ውጭ መምረጥ እንደማይችል፣ ምክንያቱ ደግሞ ከክልሉ ውጪ የሚኖረው ሕዝብ መምረጥ የሚያስችለው የሕግ መሠረት ስለሌለ መሆኑን መግለጹ ይታወሳል፡፡

የሐረሪ ክልል መስተዳድር ምክር ቤት (ካቢኔ) ሚያዚያ 3 ቀን 2013 .ም. ባካሄደው አስቸካይ ስብሰባ፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሐረሪ ብሔራዊ ጉባዔን አስመልክቶ ያስተላለፈውን ውሳኔ በሚመለከት ባደረገው ውይይት፣ የሐረሪ ክልል ምርጫ አፈጻጸምደት በክልሉ የሐረሪ ጉባዔና የፌዴራልዝብ ተወካይ ልዩ ውክልና ምርጫ፣ የመራጮች ምዝገባ እየተካሄደ እንዳልሆነና ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሚያዚያ 1 ቀን 2013 .ም. የሐረሪ ጉባዔን አስመልክቶ ያስተላለፈው ውሳኔ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መጋቢት 6 ቀን 1987 .ም. ባካሄደው 102 መደበኛ ስብሰባ ያሳለፈው ውሳኔ፣ የክልሉ ሕገ መንግሥትና የምርጫ ሕጉን በሚፃረር መንገድ የተሰጠ መሆኑን፣ ሕገ መንግሥታዊ ይዘት እንደሌለውና ከሕግ አንፃርም ተቀባይነት እንደሌለው ድምዳሜ ላይ መድረሱን ገልጿል።

ምርጫ ቦርድ ሚያዚያ 1 ቀን 2013 .ም. የሐረሪ ብሔራዊ ጉባዔ ምርጫን አስመልክቶ ያስተላለፈው ውሳኔ፣ ሕገ መንግሥትዊ፣ጋዊ፣ ፍትሐዊና አመክንዮአዊ እንዳልሆነ፣ እንዲሁም የሐረሪ ክልል ሕገ መንግሥትን ያላማከለ ስለሆነ ከሕግ አንፃር ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቋል።

የክልሉ ካቢኔ በውሳኔው የክልሉ ሕገ መንግሥትና የሕግ የበላይነት እንዲከበር፣ እንዲሁም የፌዴራልዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ያስተላለፈው ውሳኔ ሊከበር እንደሚገባና እነዚህን ችግሮች ለማረም አግባብነት ያለው አካል ተቋቁሞ ተገቢው የዕርምት ዕርምጃ እንዲደረግ መወሰኑን፣ የክልሉ መንግሥት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ጽሕፈት ቤት በማኅበራዊ ተስስር ገጹ አስታውቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...