Thursday, June 8, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ የኢኮኖሚ ጉዳይ ምክር ቤቱን ሪፖርት እያዳመጡ ነው] 

  • የምግብ ዘይት ጉዳይ በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?
  • ክቡር ሚኒስትር የፋብሪካዎች ምርት በከፍተኛ ደረጃ ተሻሽሏል።
  • አቅርቦቱስ?
  • አቅርቦቱ ላይ መቆራረጥ አለ፣ ግን መቀረፉ አይቀርም፡፡ 
  • የሲሚንቶ ጉዳይስ? 
  • ቀድሞውንም ቢሆን ሲሚንቶ በበቂ ሁኔታ ይመረታልየምርት ችግር የለም። 
  • አቅርቦቱስ?
  • አቅርቦቱ ተቋርጧል፡፡ 
  • እና ምን እያደረጋችሁ ነው? 
  • አምራቾቹ የሚያነሱት የዋጋ ጥያቄ አለ፣ ቢሆንም መፈታቱ አይቀርም።
  • ነዳጅስ? 
  • መንግሥት ያለውን የውጭ ምንዛሪ ቅድሚያ የሚሰጠው ለነዳጅ ግዥ እንደሆነ ይታወቃል።
  • ስለመታወቁ አልጠየቅኩም፣ ምርቱ በበቂ ሁኔታ እየቀረበ ስለመሆኑ ነው፡፡
  • ወደ እሱ ልገባ ነው፡፡ 
  • እሺ ግባ
  • በቂ ነዳጅ ተገዝቷል 
  • የት ነው የሚገኘው?
  • ወደ እሱ ልመጣ ነው፡፡ 
  • እሺ፡፡ 
  • ምርቱ ተገዝቶ ጂቡቲ ይገኛል፡፡ 
  • ስለዚህ የአቅርቦት ችግር የተፈጠረው ለዚህ ነው?
  • አይደለም ምርቱን ከጂቡቲ በሚጓጓዝበት ኮሪደር ግጭት በመከሰቱ በጊዜ መድረስ አልቻለም ፡፡
  • ታዲያ የአቅርቦት ችግሩን ለመፍታት ምን አደረጋችሁ? 
  • ችግሩ ጊዜያዊ ስለሆነ ነዳጁ ገብቶ ይሠራጫል ፡፡
  • ጊዜያዊ ችግሩን ለመቅረፍ ምን እንዳደረጋችሁ ነው የጠየቅኩት፡፡
  • ወደ እሱ ልመጣ ነው ክቡር ሚንስትር?
  • አንተ እስክትመጣ ይቀረፋል፡፡ 
  • ምኑ?
  • የነዳጅ ችግሩ መቀረፉ ስለማይቀር ሌላውን እንመልከት፡፡ 
  • የስንዴናዳቦ አቅርቦት ማቅረብ እችላለን፡፡ 
  • ቀጥል፡፡ 
  • መንግሥት ለስንዴ በሰጠው ትኩረት እርስዎም እንደተመለከቱት የበጋ ስንዴ ምርት ማጨድ ጀምረናል፡፡ 
  • አቅርቦቱ ላይ አተኩር፡፡
  • የስንዴ አቅርቦት ችግር በመኖሩ በዳቦ ፍላጎት ላይ ክፍተት ፈጥሯል።
  • ምን እያደረጋችሁ እንደሆነ ነው ማወቅ የምፈልገው፡፡
  • የአቅርቦት ችግሩ መፈታቱ አይቀርም እየሠራንበት ነው።
  • የሁላችሁም መልስ ችግሩ መፈታቱ አይቀርም የሚል ነውማነው የሚቀርፈው? መቼ ነው የሚቀረፈው? 
  • እሱንም ለመቅረፍ እየተመካከርን ነው።
  • ምኑን?
  • መቼና ማን ይቅረፈው የሚለውን!

[ክቡር ሚኒስትሩ እንደ አዲስ ለሚቋቋመው የመንግሥት መሥሪያ ቤት የቀረበላቸውን የተቋማዊ አደረጃጀት ረቂቅ ሰነድ እየተመለከቱ ሳለ ረቂቁን ያዘጋጀው ቡድን አባል ወደ ቢሯቸው ገባ]

  • እንደምን አሉ ክቡር ሚኒስትር?
  • ኦ… አንተ ነህ እንኳን መጣህ።
  • የተቋሙ አደረጃጅትን በተመለከተ ያዘጋጀነው ረቂቅ ሰነድ እንደደረሰዎት ተስፋ አደርጋለሁ።
  • እሱን እየተመለከትኩት ነው የመጣኸው።
  • የተለያዩ አገሮችን ተሞክሮዎች አጥንተን ለኢትዮጵያ ተስማሚ ይሆናሉ ያልናቸውን አደረጃጀቶች አካተናል።
  • ተስማሚ ተሞክሮ ነው ያልከው?
  • አዎ፣ የተጀመረውን ለውጥ ሊገልጹ የሚችሉትን ተስማሚ ተሞክሮዎችን ነው የወሰድነው፡፡
  • እርግጠኛ ነህ?
  • አይጠራጠሩ ክቡር ሚኒስትር፣ ሙሉውን ሰነድ አላዩትም እንዴ? 
  • ሙሉውን አይቼዋለሁ፣ ግን ተስማሚ ያልከውን ሳይሆን ሌሎች ነገሮችን ነው ያገኘሁት፡፡ 
  • ሌላ ምን አገኙ?
  • አስቀያሚ፡፡
  • ተስማሚ ያልሆነ አስቀያሚ? 
  • ለምሳሌ ኢንዶክትሪኔሽን፣ ዳይሬክቶሬት የሚል አደረጃጀት ምን ማለት ነው? 
  • በጥናታችን የተለያዩ አገሮች ውጤታማ የሕዝብ ግንኙነት ሥራ የተወጡበት አደረጃጀት መሆኑን ለይተናል።
  • ጥናት ነው ያልከው?
  • አዎ! እንደ ካናዳ፣ እንግሊዝና የመሳሰሉ አገሮች የተገበሩትና ውጤት ያገኙበት አደረጃጀት ነው። 
  • ጥናቱን ተወውና የቃሉን ጥሬ ትርጉም ልትነግረኝ ትችላለህ?
  • ጥሬ ቃሉን አላጠናንም፣ ነገር ግን የሕዝብ ግንኙነት ሥራ ማለት አይደል እንዴ?
  • ኢንዶክትሪኔሽን? 
  • እንደዚያ መሰለኝ፡፡
  • እሱን ነገር መቼ ነው የምትተወው ግን?
  • ምኑን?
  • መሰለኝ ደሳለኙን?
  • እየሞከርኩ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • ከምትሞክር ለምን አትፈልግም? 
  • ምን?
  • የሌላ አገር ተሞክሮ፡፡ 
  • ኮሚክ እኮ ነዎት ክቡር ሚንስትር 
  • ለማንኛውም ኢንዶክትሪኔሽን ማለት ሐሳብን ማጥመቅ ወይም ጭንቅላት ማጠብ ማለት ነው።
  • ለዚያ እኮ ነው ይህንን ተሞክሮ ለእኛ ተስማሚ ይሆናል ብለን ያመጣነው ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • ተሞክሮ ነው ያልከው?
  • አዎ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • የአገር ውስጥ ተሞክሮ ነው?
  • በአገር ውስጥም አንዳንድ ተቋማት ይጠቀሙበታል፣ እኛ ግን የካናዳን… 
  • እንዳትጨርሰው፡፡
  • አልቋል…ግን ትቼዋለሁ፡፡ 
  • ቢገባህ ይህንን አደረጃጀት ልትደግመው ይቅርና ከሌሎች ተቋማት ጭምር ታስቀር ነበር፡፡ 
  • ኃላፊነቱን ከሰጡኝ እችላለሁ፡፡ 
  • የማን ኃላፊነት ነው እሱን አደረጃጀት የማስቀረት፡፡ 
  • መጀመርያ ከራስህ ጀምር፡፡ 
  • ከየት?
  • ከዚህ ሰነድ ላይ፡፡ 
  • ጥሩ እንዳሉት አደርጋለሁ፡፡ 
  • ተወው እንዲያውም፡፡ 
  • ለምን ክቡር ሚኒስትር?
  • በድጋሚ ይሠሩታል፡፡ 
  • ማን ይሠራዋል?
  • ባለሙያ፡፡ 
  • እይሆንም ክቡር ሚኒስትር፣ ለባለሙያ ኃላፊነት ሊሰጡ? 
  • ሌላ ቦታ እስክታገኝ ውጣ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

በኦሮሚያ ክልል በስድስት ከተሞች የተዋቀረውን ሸገር ከተማን የማደራጀት ሥራ ተጀመረ

በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ ስድስት ከተሞች የተዋቀረው ሸገር ከተማን...

የኦሮሞን ሕዝብ ታሪክ አልባ በማድረግ ታሪክ አይሠራም

በኢተፋ ቀጀላ​​  ከዛሬ ሃምሳ ዓመት ወዲህ ከተፈጠሩት የኦሮሞ ድርጅቶች መካከል ከኢጭአት በስተቀር፣...

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው አሠራር ወጣ ያለውን ‹‹የወደፊት ግብይት›› ሥርዓት በይፋ አስጀመረ

የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከተለመደው የማገበያየት ተግባሩ ወጣ ያለና በኢትዮጵያ...

የባንክ ማቋቋሚያ መሥፈርት እንደሚጠነክር ሚኒስትሩ ተናገሩ

 ባንኮች ስለውህደት እንዲያስቡም መክረዋል በኢትዮጵያ ውስጥ ባንክ ለማቋቋም የሚያስፈልገው መሥፈርት...

ማን ይቻለን?

በጠዋት የተሳፈርንበት ታክሲ ውስጥ በተከፈተው ሬዲዮ፣ ‹‹ይኼኛው ተራራ ያን...

በኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት አንድ ድንጋይ ደጋግሞ እንዳይመታን

ከጣሊያን ቅኝ ተገዥነት በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመን በኮንፌዴሬሽን፣ ቆየት ብሎም እንደ አንድ የኢትዮያ ግዛት አካል የነበረችው ኤርትራ ከደርግ ሥርዓት መውደቅ በኋላ ነፃ አገር ሆናለች፡፡ ነፃ አገር መሆንና ከኢትዮጽያ ጋር መቀጠል በወቅቱ ብዙ ሲባልለት የነበረ ጉዳይ ነበር፡፡
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ አመሻሹን መኖሪያ ቤታቸው ሲደርሱ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈው የማዕከላዊ ኮሚቴ ገለጻ እየተከታተሉ አገኟቸውና አጠገባቸው ተቀምጠው የደረሱበትን አብረው መከታተል እንደጀመሩ፣ ባለቤታቸው ቴሌቪዥኑን ትተው መጠየቅ...

እኔ ምለው? እሺ... አንቺ የምትይው? የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ላይ አባላት እንዲያወሩ ወይም እንዲጠይቁ አይፈቀድም እንዴ? እንዴት ይከለከላል? ታዲያ ለምንድነው ፕሬዚዳንቱ ብቻ የሚያወሩት? እያወሩ አይደለም፣ ገለጻ እያደረጉ ነው። ቢሆንም አንድም አባል...

[ክቡር ሚኒስትሩ አምሽተው ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው ‹‹ፈተናዎችን ወደ ዕድል በመቀየር ሕዝባችንን እናሻግራለን›› የሚለውን የቴሌቪዥን ዜና ተመልክተው ለብቻቸው ሲስቁ አገኟቸው]

ስልክ እያወራሽ ነበር እንዴ? ኧረ በጭራሽ... ምነው? ታዲያ ምንድነው ብቻሽን የሚያስቅሽ? አይ... በቴሌቪዥኑ የሚቀርበው ነገር ነዋ። ምንድነው? ድሮ ድሮ ዜና ለመስማት ነበር ቴሌቪዥን የምንከፍተው፡፡ አሁንስ? አሁንማ ቀልዱን ተያይዘውታል... አንተ ግን በደህናህ...

[ክቡር ሚኒስትሩ የቢሮ ስልካቸው ጠራ። ደዋዩ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ኃላፊ እንደሆኑ ሲነገራቸው የስልኩን መነጋገሪያ ተቀበሉ]

ሃሎ፡፡ እንዴት አሉ ክቡር ሚኒስትር። ደህና ነኝ። አንተስ? አስተዳደሩስ? ሕጋዊ ሰውነታችን ተነጥቆ እንዴት ማስተዳደር እንችላለን ክቡር ሚኒስትር? ለዚህ ጉዳይ እንደደወልክ ገምቻለሁ። ደብዳቤም እኮ ልከናል ክቡር ሚኒስትር፡፡ አዎ። ሁለት ደብዳቤዎች ደርሰውኛል።...