Monday, September 25, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲዎች በተናጠል በጀት ማከፋፈል መጀመሩን አስታወቀ

ምርጫ ቦርድ ለፖለቲካ ፓርቲዎች በተናጠል በጀት ማከፋፈል መጀመሩን አስታወቀ

ቀን:

በአዲስ አበባናኦሮሚያ 28 ንዑስ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲከፈቱ ወሰነ

መንግሥት ለፖለቲካ ፓርቲዎች ከፈቀደው የበጀት ድጋፍ ውስጥ በእኩል የሚከፋፈለውን የተወሰነ ድርሻ፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለፓርቲዎች በተናጠል ማከፋፈል መጀመሩን አስታወቀ። 

ምርጫ ቦርድ መንግሥት ከመደበው የፓርቲዎች የበጀት ድጋፍ ውስጥ የተወሰነውን ድርሻ ለሁሉም ሕጋዊ ፈቃድ ላላቸው ፓርቲዎች የሚከፋፈልበትን ሥርዓት ያመቻቸ መሆኑን፣ በዚህም መሠረት 24.6 ሚሊዮን ብር ለሁሉም ፈቃድ ያላቸው ፓርቲዎች እንዲከፋፈል መወሰኑንና በዚህም አግባብ ከተጠናቀቀው ሳምንት ጀምሮ ለፓርቲዎች ማከፋፈል መጀመሩን ቦርዱ አስታውቋል። 

ለሁሉም ፓርቲዎች በእኩልነት እንዲከፋፈልተመደበው 24.6 ሚሊዮን ብር ለሁሉም ሕጋዊ ፈቃድ ላላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች በተናጠል 483,452 ብር ማከፋፈል መጀመሩን የገለጸው ቦርዱበጀቱን ማከፋፈል ከተጀመረበት ቀን አንስቶም 32 ፓርቲዎች ክፍያ መፈጸሙን አስታውቋል።

እስከ ዘንድሮ ድረስ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ 107 የፖለቲካ ፓርቲዎች ይንቀሳቀሱ የነበረ ሲሆን፣ በአዲሱ የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች አዋጅ መሥፈርቶችን በማሟላት ሕጋዊ ዕውቅና ማግኘት የቻሉት ግን 53 መሆናቸውን የቦርዱ መረጃ ያመለክታል፡፡ 53 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል ዘንድሮ ለሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ ለመወዳደር አመልክተው የምርጫ ምልክት የወሰዱ 49 ፓርቲዎች ናቸው። 

ነገር ግን ሁለት ፓርቲዎች በተለያዩ ምክንያቶች ከውድድሩ ራሳቸውን በማግለላቸው፣ በአሁኑ ወቅት ለምርጫ ውድድር የቀረቡት 47 የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው። 

ተግባራዊ መሆን በጀመረው አዲሱ የምርጫና የፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ፣ መንግሥት ከራሱ ካዝና፣ ከውጭ ድጋፍ፣ እንዲሁም በአገር ውስጥ ከሚገኝ ድጋፍ ለፖለቲካ ፓርቲዎች በጀት እንዲያዘጋጅ እንዲያደርግ ይደነግጋል፡፡

መንግሥት ለፖለቲካ ፓርቲዎች የሚመድበው የበጀት ድጋፍ በምርጫ ቦርድ አማካይነት የሚከፋፈል ሲሆንምርጫ ቦርድ የተለያዩ መሥፈርቶችን መነሻ ያደረገ ቀመር በማዘጋጀት የበጀት ድጋፉን የማከፋፈል ሥልጣን በአዋጁ ተሰጥቶታል። 

የማከፋፈያ ቀመሩን ለማዘጋጀት መነሻ ከሆኑት መሥፈርቶች መካከል፣ ፓርቲዎቹ ቀደም ብሎ በነበረው ምርጫ ያገኙት የመራጮች ድምፅ ቁጥር፣ ከአባላትናደጋፊዎች የሚሰበስቡት የገቢ መጠን፣ ለምርጫ በሚያቀርቧቸው ሴት ዕጩዎች ብዛት፣ በፓርቲው ውስጥ ባሉ ሴት አባላትና አመራሮች ብዛት የመሳሰሉት ይጠቀሳሉ። 

ምርጫ ቦርድ ዘንድሮ ለሚያስፈጽመው ምርጫ ለሕዝብ የተወካዮች ምክር ቤት ካቀረበው 3.7 ቢሊዮን ብር በጀት ውስጥ 2.5 ቢሊዮን ብር 2012 ዓ.ም. ፀድቆለት እንደነበር ይታወሳል፡፡ በኮቪድ ወረርሽኝ መከሰት ምክንያት ምርጫው ወደ ዘንድሮ ከተሸጋገረ በኋላ የወጪ ፍላጎቱ በመጨመሩ 1.1 ቢሊዮን ብር በተጨማሪነት እንዲመደብለት ጥያቄ አቅርቦ የፓርላማውን ውሳኔ በመጠባበቅ ላይ መሆኑን፣ ከጥቂት ሳምንታት በፊት መዘገባችን ይታወሳል። 

ከመንግሥት ከተመደበለት በጀት በተጨማሪ ከተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የልማት ፕሮግራም (ዩኤንዲፒ) በዓይነት 40,004,000 ዶላር ድጋፍ የሚደረግለት ሲሆን፣ የዚህም ዓላማ ቦርዱን ብቁ፣ ግልጽና የሚታመን ተቋም ለማድረግና አካታች፣ ግልጽና ተዓማኒነት ያለው ምርጫ ማድረግ እንዲችል ለማገዝ ነው፡፡

በሌላ ዜና ምርጫ ቦርድ ቀደም ብሎ በአዲስ አበባ ከተማና በኦሮሚያ ክልል እንዲቋቋሙ ከፈቀደው የምርጫ ጣቢያዎች በተጨማሪ፣ በአዲስ አበባ 15 እና በኦሮሚያ 13 በድምሩ 28 ንዑስ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲቋቋሙ በዚሁ ሳምንት ወስኗል። 

በምርጫ ሕጉ መሠረት አንድ የምርጫ ጣቢያ የሚያስተናግደው ከፍተኛው የመራጮች ቁጥር 1‚500 መሆን እንዳለበት የሚደነግግ ሲሆንበአዲስ አበባና በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ የተወሰኑ የምርጫ ጣቢያዎች ከተጠቀሰው ቁጥር በላይ የመራጮች የምዝገባ ፍላጎት በመታየቱ ነው ንዑስ የምርጫ ጣቢያዎቹ እንዲቋቋሙ የወሰነው።

በየትኛውም አካባቢ ተመሳሳይ ሁኔታ በቀጣይ የሚታይ ከሆነ፣ ተጨማሪ ንዑስ የምርጫ ጣቢያዎች እንዲቋቋሙ ሊወስን እንደሚችልም ቦርዱ አስታውቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የቤት ባለንብረቶች የሚከፍሉትን ዓመታዊ የንብረት ታክስ የሚተምን ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጀ

በአዋጁ መሥፈርት መሠረት የክልልና የከተማ አስተዳደሮች የንብረት ታክስ መጠን...

እንደ ንብረት ታክስ ያሉ ወጪን የሚያስከትሉ አዋጆች ከማኅበረሰብ ጋር ምክክርን ይሻሉ!

የመንግሥትን ገቢ በማሳደግ ረገድ አስተዋጽኦ እንዳላቸው የሚታመኑት የተጨማሪ እሴት...

ለዓለምም ለኢትዮጵያም ሰላም እንታገል

በበቀለ ሹሜ ያለፉት ሁለት የዓለም ጦርነቶች በአያሌው የኃያል ነን ባይ...