Wednesday, October 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናፓርላማው ሕወሓትና ኦነግ ሸኔን በአሸባሪነት ለመፈረጅ በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ሐሙስ ይወያያል

ፓርላማው ሕወሓትና ኦነግ ሸኔን በአሸባሪነት ለመፈረጅ በቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ላይ ሐሙስ ይወያያል

ቀን:

የሚኒስትሮች ምክር ቤት ቅዳሜ ሚያዝያ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. ሕወሓትና ኦነግ ሸኔ የተባሉ ድርጅቶች በአሸባሪነት እንደፈረጁ ባሳለፈው የውሳኔ ሐሳብ ላይ፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሐሙስ ሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ውሳኔ ለመስጠት እንደሚሰበሰብ ተገለጸ፡፡

ምክር ቤቱ በላከው መግለጫ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ተወያይቶ ባሳለፈው ውሳኔ ሐሳብ ላይ የተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ለሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ቀጠሮ የያዘ ሲሆን፣ ባለፈው ዓመት በወጣው የፀረ ሽብር አዋጅ መሠረትም በአሸባሪነት እንዲፈረጅ የውሳኔ ሐሳብ የቀረበበት ድርጅት ወይም ግለሰብ ራሱን የመከላከል መብት እንዲሰጠው የሚደነግገውን አንቀጽን በመጥቀስ፣ የውሳኔ ሐሳብ የቀረበባቸው ድርጅቶች የቀረበውን ውሳኔ ሐሳብ ለማስቀረት ያስችላል ያሏቸውን መከላከያዎች በአካል ቀርበው እንዲያስረዱ የ48 ሰዓት ጊዜ ገደብ መስጠቱን አስታውቆ ነበር፡፡

ሚያዝያ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. በሚደረገው ውይይት ምክር ቤቱ የውሳቤ ሐሳቡን ተቀብሎ የሚያፀድቀው ከሆነ፣ መንግሥት በእነዘህ ድርጅቶች ውስጥ በአመራርነትና በአባልነት የሚያገለግሉ ግለሰቦች በአሸባሪነት ለመጠየቅ የሚያስችለው ይሆናል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የተጠቀሱት ድርጅቶና የድርጅቶቹ አመራሮች ሀብትን ለመውረስ እንዲችል የፀረ ሽብር አዋጅ ይደነግጋል፡፡ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ ከሳምንታት በፊት መግለጫ ከሕወሓት አመራሮችና ግንኙነት አላቸው ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች የባንክ ሒሳብ ውስጥ የሚገኝ 6.7 ቢሊዮን ብር እንዲታገድ ማድረጉን ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በሕወሓት ባለቤትነት ሥር የነበረውን ኤፈርት የተባለ ኢንዶውመንት ሀብቶች፣ በፌዴራል መንግሥት ሥር በተቋቋመ ባለአደራ አስተዳደር ሥር እንዲተዳደር መወሰኑ አይዘነጋም፡፡

ይሁን እንጂ የፀረ ሽብር ፍረጃውን መሠረት አድርጎ ከላይ የተገለጹትን ሀብቶች መንግሥት መውረስ ይችላል የሚለው ጥያቄ የሕግ ክርክር ከወዲሁ ፈጥሯል፡፡  

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን የሚተላለፈውን ዜና በመገረም እየተመለከቱ አገኟቸው]

ምንድነው እንዲህ ቀልብሽን የሳበው? ስለሰላም ኖቤል ሽልማት ዜና እየተመለከትኩ ነበር። እና...

የወሎ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ መመሥረትና የአማራ ክልል ጥያቄ

አማራ የኢሕአዴግ አንዱ መሥራችና አጋር ከሆነው ብሔረ አማራ ዴሞክራሲያዊ...

የሽንኩርት ዋጋ ሰማይ የነካበት ምክንያት ምንድነው?

ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት የሸማቾችን ኪስ ካስደነገጡ መሠረታዊ ከሚባሉ...

የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ኤግዚቢሽን ማዕከልን እንዲያስተዳድር የተሰጠው ኮንትራት ለምን ተቋረጠ?

በአዲስ አበባ ከተማ ለንግድ ትርዒት ዝግጅት ብቸኛ በመሆን የሚጠቀሰው...