Saturday, December 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

ጊዜው አሁን ነው! ከነባራዊ ተግዳሮቶች በመነሳት የጀርመን ሰብዓዊ የድጋፍ ሥራዎች በኢትዮጵያ

ሽቴፋን አወር

ለፈው ክረምት አንስቶ የጀርመን አምባሳደር ሆኜ ቆይታዬን ስጀምር ገሪ እጅግ ከባድ የሰብዓዊ ችግሮች እያየች የነበረችበት ሁኔታ ነበር። የኮቪድ-19 ወረርሽኝ፣ የበረሃ አንበጣና ጎርፍ በአብዛኛው የገሪቱ አካባቢዎችና ክልሎች የሰብዓዊ ድጋፍ ፍላጎቶችን ጨምረው ነበር። በትግራይ የተከሰተው ግጭትም በነበሩት ተግዳሮቶች ላይ ተጨማሪ ጫና ሆኗል። በትግራይ በትንሹ 4.5 ሚሊን የሚሆኑ ሰዎች የምግብ ርዳታ ያስፈልጋቸዋል ተብሎ ይታመናል። ከእነዚህም ውስጥ አብዛኞቹ የሰብዓዊ ርዳታ ተደራሽነት የላቸውም። እየተቃረበ ያለ የረብ አደጋን የሚያሳዩ ምልክቶች ከፍተኛ ትኩረት ሊሰጣቸው ይገባል። በትግራይ ያሉ አርሶ አደሮች ከክረምቱ መግቢያ በፊት ማሳቸውን ማረስ ካልጀመሩ ክልሉ  እ... 1980ዎቹን የሚያስታውስ የረሃብ አደጋ ሊያጋጥመው ይችላል።

ይህ ቀውስ ከጀመረ አንስቶ ጀርመን ከአውሮፓ ብረትና ከሌሎች የሰብዓዊ ርዳታ ለጋሾችና አጋሮች ጋር በመሆን ያልተገደበ የሰብዓዊ ርዳታ ተደራሽነትና የሲቪሎች ጥበቃ እንዲኖር ስትጠይቅ ቆይታለች። ይህን መጠየቃችንም የሚቀጥል ይሆናል። ያም ሆኖ በተመሳሳይ ዜ የሰብዓዊ ርዳታ ራችንን በፍጥነት እንዲሁም በከፍተኛ ሁኔታ ጨምረናል። እ.ኤ.አ. በኖቬምበር 2020 ጀርመን ለቀውሱ ምላሽ የሚሆን ስድስት ሚሊዮን ዶላር ለኢትዮጵያ የሰብዓዊ ርዳታዎች ፈንድ መድባለች። በተጨማሪም ለዚሁ ላማ የሚውል ተጨማሪ አሥር ሚሊዮን ዶላር መድበናል። ባለፈው መት ለኢትዮጵያ ሰብዓዊ ርዳታዎች ፈንድ ከቀረቡ ልገሳዎች ውስጥ ትልቁ ድርሻ የእኛ ነበር። በአጠቃላይ ጀርመን እ.ኤ.አ. በ2020 ከ40 ሚሊዮን ዶላር በላይ በኢትዮጵያ ለተከናወኑ የሰብዓዊ ርዳታዎች ያወጣች ሲሆን ይህንንም ድጋፋችንን በዚህ መት ይበልጥ ማሳደግ ቅዳችን ነው።

ግባችን ግልጽ ነው፡፡ በትግራይ እንዲሁም ከዚያ ባሻገር ያሉ ቃዮችን ማብረድ እንዲሁም ማንም ሰው ወደኋላ ሳይቀር ይወትን ማዳን ነው። መሬት ላይ ያለው ሁኔታ አሁንም ተለዋዋጭና ከባድ ነው። ነገር ግን የሰብዓዊ ርዳታ አጋሮችን ጨምሮ የመንግታቱ ድርጅት እንዲሁም መንግታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ከዚህ ቀደም እንዲሁም በተለያዩ ሮች እጅግ አስቸጋሪ በሚባሉ ሁኔታዎች ውስጥ ኃላፊነታቸውን መወጣት እንደሚችሉ አስመስክረዋል። ከኢትዮጵያ መንግት ጋር በቅርበት በመተባርና አስፈላጊውን የፋይናንስ ድጋፍ በማቅረብ፣ ለጥበቃቸው የምንችለውን ሁሉ በማድረግና ርዳታ የሚሹትን ሁሉ መድረስ እንዲችሉ በማገዝ እነዚህን ድርጅቶች በተሻለ ልንደግፋቸው እንችላለን።

በዚ አጋጣሚ መንግት ላደረጋቸው ከፍተኛ ራዎችና ለደረሰበት ደት ለምሳሌ የሰብዓዊ ርዳታ ተደራሽ የሚሆንበትን  መንገድ መክፈት፣ ተፈጽመዋል ስለተባሉ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ወይም የጦር ወንጀሎች ገለልተኛ ምርመራን መፍቀድ፣ እንዲሁም የኤርትራ ኃይሎች ለቀው እንዲወጡ ስለተደረገው ስምምነት ውቅና መስጠት እፈልጋለ። ነገር ግን የተባበሩት መንግታት ድርጅት መሬት ላይ ያለው የሰብዓዊ ሁኔታ እየተሻሻለ እንዳልሆነ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል። እየባሰም ነው። ስለዚህ እንቅስቃሴዎቻችንን በጥምረት ማሳደግ እንዲሁም በሚሊተሪና ሲቪል መካከል ያለውን ቅንጅት ማሻሻል ይኖርብናል። መንግታዊ ባልሆኑ ድርጅቶችና ራተኞቻቸው ላይ የተቃጡ ጥቃቶች መመርመር አለባቸው።

እ.ኤ.አ. በ2021 የምናደርገው የሰብዓዊ ድጋፍ ከትግራይ ው ያሉ ሰዎችንም ተደራሽ የሚሆን ይሆናል። ይህንንም የምናደርገው አጋሮቻችን ከፍተኛውን ርዳታ የሚሹ ሰዎች ባሉበት ፍራዎች በጀት መድበው ራዎችን ይሩ ዘንድ የሚያስፈልጋቸውን ሁኔታዎች በማመቻቸት ነው። ወደ 20 ከሚጠጉ የተለያዩ የመንግታቱ ድርጅት ኤጀንሲዎች እንዲሁም ለም አቀፍ ድርጅቶች ጋር በአጋርነት እንሠራለን፡፡ የምናተኩርባቸው ሴክተሮች ምግብ፣ ጤና ጥበቃ፣ መጠለያ እንዲሁም ውና ንህናን ያካትታሉ።

ለምሳሌ ለም የምግብ ፕሮግራም በሚያከናውናቸው የምግብ ድጋፍ ራዎች የምናግዝ ሲሆን የመንግታቱ ድርጅት የምግብና እርሻ ድርጅትን ደግሞ የበረሃ አበጣን ለመከላከል በሚያደርገው ጥረት እናግዛለን፡፡ በተጨማሪም የሴቭ ዘ ችልድረን ሕፃናትን የመጠበቅ ራዎች እንዲሁም የጀርመኑን ቬልት ንገር ሂልፈ (Welthungerhilfe) የአስቸኳይ ዜ ድጋፍና የንፁህ ው ተደራሽ ለማድረግ የሚያደርገውን ጥረት እንደግፋለን፡፡

ለም አቀፍ ደረጃ ወደ 2.5 ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ ለሰብዓዊ ርዳታዎች እ.ኤ.አ. በ2021 የበጀት መት በመመደብ ጀርመን ከለም ሁለተኛዋ የሰብዓዊ ርዳታዎች ለጋሽ ነች። የገንዘቡ መጠን ባለፉት አምስት መታት ከሁለት እጥፍ በላይ አድጓል። በዚህም ምክንያት በለም ዙሪያ በግጭት፣ ተፈጥሮ አደጋዎች አልያም ወረርሽኞች የሚጠቁ ሰዎችን እየረዳን ያለን ሲሆን ይህን ጥረታችንንም የውጭ ፖሊሲያችንና የለም አቀፍ ኃላፊነታችን ወሳኝ አካል አድርገን እናየዋለን።

በየትኛውም የለም ክፍል ቢሆን የሰብዓዊ ርዳታ የሚቀርበው የሰብዓዊነት፣ ኢጣልገብነትገለልተኛነትና የነነት መርሆችን መረት ባደረገ መንገድ ነው። በዚህ ረገድ አንድ ቁልፍ መርህ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው የትም ይሁኑ የት ርዳታ መድረስ ያለበት እጅግ በጣም ለሚያስፈልጋቸው ነው የሚለው ነው። ይህ ከፍተኛ ቁጥር ካላቸው በገር ውስጥ ከተፈናቀሉ ሰዎች ብዛት ጋር ተያይዞ ትልቅ ተግዳሮት ነው። ነገር ግን እነህ መሪ መርሆች በገሪቱ ውስጥ በተለይም በትግራይ ያሉ ተግዳሮቶችን ለማስተናገድ ቁልፍ ናቸው ብዬ በኑ አምናለ። ለድርጊት ዜው አሁን ነው፡፡ ለዚህም ጀርመን ከኢትዮጵያ መንግ እንዲሁም ከለም አቀፍ አጋሮቿ ጋር በቅርብ ትብብር ድርሻዋን ለመወጣት ዝግጁ ናት።

ከአዘጋጁ፡- ጸሐፊው በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር ሲሆኑ ጽሑፉ የእሳቸውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_imgspot_img
- Advertisment -

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

Related Articles