Saturday, April 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትአልጄሪያዊው ሙስጠፋ ባህራፍ በድጋሚ የአኖካ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

አልጄሪያዊው ሙስጠፋ ባህራፍ በድጋሚ የአኖካ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመረጡ

ቀን:

በግብፅ ካይሮ በተካሄደው የአፍሪካ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር (አኖካ) 19ኛ ጠቅላላ ጉባዔና ምርጫ ላይ አልጄሪያዊው ሙስጠፋ ባህራፍ በድጋሚ ፕሬዚዳንት ሆነው ተመርጠዋል፡፡

በምርጫው ሒደት በ38 ድምፅ ያሸነፉት አልጀሪያዊው ሙስጠፋ ባህራፍ ለቀጣዩ አራት ዓመታት አኖካን በፕሬዚዳንትነት ያስተዳደራሉ፡፡ ተፎካካሪ ሆነው ለምርጫ የቀረቡትና 15 ድምፅ ያገኙት ሩዋንዳዊቷ ሊዲያ ኒስካራ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ (ዶ/ር)፣ ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዚዳንቷ ኮማንደር ብርሃኔ አደሬና ዋና ጸሐፊው አቶ ዳዊት አስፋው በአኖካ ጉባዔ ላይ መታደማቸውን ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴው ገልጿል፡፡

ከሳምንታት በፊት ባካሄደው የአኖካ ዞን አምስት አገሮች ብሔራዊ ኦሊምፒክ ኮሚቴዎች ማኅበር ምርጫ አሸብር ወልደ ጊዮርጊስ (ዶ/ር) ፕሬዚዳንት አድርጎ መምረጡ ይታወሳል፡፡    

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተወግዘው የነበሩ ሦስቱ ሊቀጳጳሳትና 20 ተሿሚ ኤጲስ ቆጶሳት ውግዘት ተነሳ

_ቀሪዎቹ ሦስት ህገወጥ ተሿሚዎች የመጨረሻ እድል ተሰጥቷቸዋል ​ ጥር 14...

በሕወሓት አመራሮች ላይ ተመስርቶና በሂደት ላይ የነበረው የወንጀል ክስ ተቋረጠ

በቀድሞ የትግራይ ክልል ፕሬዚደንት ደብረጽዮን ገብረሚካኤ,(ዶ/ር)ና ባለፈው ሳምንት በተሾሙት...

[የምክር ቤቱ አባል ላቀረቡት ጥያቄ በተሰጣቸው ምላሽ አቤቱታቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር ትክክል ነው? ምነው? ምክር ቤቱም ሆነ...

የጉራጌ የክልልነት ጥያቄ ትኩሳት

ቅዳሜ መጋቢት 16 ቀን 2015 ዓ.ም. በጉራጌ ዞን ወልቂጤ...