Saturday, December 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅአያዎ

አያዎ

ቀን:

ግማሽ ሰው – ግማሽ ምንትስ

ሳልጓዝ ሄጃለሁ – እየሄድኩ አልሄድኩም

ሳልሰማ ሰምቻለሁ – ሰምቼ አልሰማሁም

ሳላነብ አንብቤያለሁ – አንብቤ አላነበብኩም

ሳልዳስስ ዳስሻለሁ – ዳስሼ አልዳሰስኩም

ሳልጠጣ ጠጥቻለሁ – አልረካሁ ጠጥቼ

ሳልበላ ጠግቤያለሁ – አልጠገብኩ በልቼ

ሳላይ አይቻለሁ – አላየሁ አይቼ

ሳለብስ ለብሻለሁ – አልሞቀኝ ለብሼ

በእጄ ምንም የለ – ሸቀጥ አግበስብሼ፡፡

በዶላርና በዩሮ – በፓውንድ ተሞልቶ

ኪሴ ባዶ ሆኗል – ባዶው ኪሴ ሞልቶ

ከሻርኩኝ ቆየሁኝ – በምናብ መኖርን – የምናብን ደስታ

ዳንሰኛ ሆኛለሁ  – በዘመኑ ዚቅ በእሽክለኬንታ

ዝም ብዬ ፈሳለሁ – በግብስብስ ቱቦ

ሚዛንና ዓርማዬ – የቁስ ቅራንቅቦ

መድረሻዬ የት ይሆን? – የጉዞዬ አቅጣጫ

ወደ ፀሐይ መግቢያ – ወይ ወደ ፀሐይ መውጫ

ከቶ ምን ይሆን – ማምለጫ ከኅሊና

እስቲ ተጠየቁ  –  በችሎት ቁሙና

ተለዋውጠውብኝ  – ኅሊና እና ሆዴ

‘’ሰውየው እኔ ነኝ ወይ?’’ – ኧረ ፈላ ጉዴ፡፡

  • ዕዝራ ኃይለ ማርያም መኰንን
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...