Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅይከርቸም ኅሊናዬ

ይከርቸም ኅሊናዬ

ቀን:

ይታሸግ አእምሮዬ – ይዘጋ ምላሴ

በዝምታ አርፎ  – ደስ እንዲለው ነፍሴ፡፡

ክፉ እንዳያዩ – ዓይኖቼ ይጨልሙ

ከንፈሮቼ ይታሸጉ – ሰውን እንዳያሙ፡፡

እንቶ ፈንቶ እንዳይሰሙ – ይደፈኑ ጆሮዎቼ

ክፉ ቦታ እንዳይሔዱ  –  ወርች ይግቡ እግሮቼ፡፡

እጆቼ ይታሰሩ  – እንዳይገቡ እዳ

በሰው ደም በመስቃ- እንዳይገቡ ፍዳ፡፡

ጥጥ ይወተፍበት – በአፍንጫዬ ቀዳዳ

ሰርን በሚበጥስ – ሽታ እንዳይፈነዳ፡፡

ምንም እንዳያኝኩ – ጥርሶቼ ይውለቁ

ከርሀብተኛ ነጥቀው – ምግብ እንዳያኝኩ፡፡

በመስረቅ በውሸት – በመግደል በዘረፋ

በራሴ ዘውድ ጭኖ- ከምሆን አኪላፋ

ነፍሴን አቀጭጮ- ስጋዬን ከሚያፋፋ

ይከርቸም ኅሊናዬ – ዝም ብሎ ያንቀላፋ፡፡

  • ዕዝራ ኃይለማርያም መኰንን
spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...