Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበኮሮና ወረርሽኝ የመያዝና በቫይረሱ የመሞት ምጣኔ መቀነሱ ተነገረ

በኮሮና ወረርሽኝ የመያዝና በቫይረሱ የመሞት ምጣኔ መቀነሱ ተነገረ

ቀን:

በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝ የመያዝና የሞት ምጣኔ መቀነሱን የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት አስታወቀ፡፡

ኢንስቲትዩቱ ይህን ያስታወቀው ዓርብ ሰኔ 4 ቀን 2013 .ም. ከሳይንስና ከፍተኛ ትምህርት ሚኒስቴርናጤና ሚኒስቴር ጋር 15 ወራትጋት ሆኖዘለቀው የኮሮና ወረርሽኝ ላይ የተደረጉ የምርምር ጥናቶች በቀረበበት ወቅት ነው፡፡

የወረርሽኙ አሁናዊ የሥርጭትና የሞት ምጣኔ ማዕበሉ የመውጣትና የመውረድ ሁኔታ ያለው መሆኑን የጠቆሙት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር  አቶ አስቻለው ዓባይነህ፣ በድጋሚ ሥርጭቱ እንዳያሻቅብ አሁንም ጥንቃቄ ወሳኝ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

‹‹የወረረሽኙርጭት ከፍና ዝቅ ማለት የተለመደ ቢሆንም፣ እንደ ሌሎች አገሮች ዋጋ እንዳያስከፍለን ቅድመ መከላከል ላይ ኅብረተሰቡ መበርታት አለበት፤›› ብለዋል፡፡

በአትዮጵያ በ2012 .ም. የትንሳዔ በዓል ግብይት ወቅ ማኅበረሰቡ  ጥንቃቄ ባለማድረጉ፣ነሐሴ ወር በተደረገው የዳሰሳ ጥናት ወረርሽኙ ተዛምቶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ አሁንም ያለው የኮሮና ቫይረስ ሥርጭት ዝቅ ሲል ይዞ የሚመጣው የወረርሽኝ ማዕበል ከፍ ሊል ይችላል ብለዋል፡፡

ስለዚህ የሚከናወኑይማኖታዊፖለቲካዊ መሰባሰቦች የሥርጭት ምጣኔውን ከፍ ስለሚደርጉ፣ አሁንም መሰባሰብን መቀነስ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

በተጨማሪም ማኅበረሰቡ ስለቫይረሱ ያለው ግንዛቤ 99 በመቶ መድረሱን፣ ለዚህም 34 በመቶ ከሬዲዮ፣ 47 በመቶ ከቴሌቪዥን፣ 20 በመቶ ከማኅበራዊ ድረ ገጾችና አምስት በመቶ ደግሞ ከሃይማኖት ተቋማት መሆኑን በጥናት መረጋገጡን አቶ አስቻለው ተናግረዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...