Saturday, December 9, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበምርጫው ዋዜማ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች ጥብቅ ቅኝት እያደረጉ ነው

በምርጫው ዋዜማ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ የጸጥታ ኃይሎች ጥብቅ ቅኝት እያደረጉ ነው

ቀን:

ሰኞ ሰኔ 14 ቀን ጠዋት የሚካሄደው አጠቃላይ ምርጫ ያለ ጸጥታ ችግር እንዲከናወን ኋላፊነት የወሰዱ የጸጥታ ኃይሎች በምርጫው ዋዜማ በአዲስ አበባ ጎዳናዎች ላይ ቅኝት እያደረጉ ነው። 

በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የፌዴራል ፖሊስ ፣ የአዲስ አበባ ፖሊስ አባላት እንዲሁም የመከላከያ ሠራዊት እና የሪፐብሊክ ጋርድ (ጥበቃ) አባላት በተለያዩ ተሽከፍካሪዎች ላይ ሆነው ቅኝት ሲያደርጉ ከቅዳሜ ምሽት ጀምሮ ተስተውለዋል። 

በምርጫው ዋዜማ እሁድ የጸጥታ አስከባሪዎች ቅኝት በሰፊው የተስተዋለ ሲሆን ፤ ለወታደራዊ እንቅስቃሴ ምቹ እና ፈጣን የሆኑ ባለአራት እግር ሞተር ሳይክል ተሽከርካሪዎች ላይ ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ የሚያውለበልቡ የሪፐብሊክ ጥበቃ አባላት በከተማዋ አንዳንድ አካባቢዎች በተለይም በሽሮሜዳ ፣ ስድስት ኪሎ ፣ ፒያሳ አካባቢዎች ሲዘዋወሩ ተስተውለዋል።

የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ብርቱካን ሚደቅሳ ቅዳሜ ሰኔ 12 ቀን ለጠቅላይ ሚንስትሩ በጻፉት ደብዳቤ አስተዳደራቸው ቀዳሚ ትኩረቱን በምርጫ ጸጥታ ጉዳይ ላይ እንዲያደርግ እንዲሁም የአየር ትራንስፖርትን ያካተተ የትራንስፖርትና የሎጀስቲክስ አቅርቦት ለአስቸኳይ ሁኔታዎች ዝግጁ እንዲሆን ጠይቀዋል።

ጠቅላይ ሚንስትር አብይ አህመድ (ዶ/ር) እሁድ ሰኔ 13 ቀን ብሔራዊ የምርጫ ደህንነት እዝ አባላትን በመሰብሰብ የተደረገውን ዝግጅት እንደገመገሙ የጠቅላይ ሚንስቴር ጽ/ቤት መረጀ ያመለክታል። 

በዚህ ግምገማም ከጽጥታ ኃይሎች ስምሪት በተጨማሪ ፤ በድሮን እና በሳተላይት የታገዘ የምርጫ የደህንነት ቅኝት በመላ የሀገሪቱ እየተከናወ ስለመሆኑ ገለጻ መደረጉን የጽ/ቤቱ መረጃ አመልክቷል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...