Friday, December 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
እኔ የምለዉዲፕሎማሲ - ዓብይና ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ

ዲፕሎማሲ – ዓብይና ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ

ቀን:

መስፍን ብቱ

ሰኞ ለት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለፓርላማው ባደረጉት ንግግር ውስጥ ካነሷቸው ነጥቦች አንደኛው የዲፕሎማሲው ጉዳይ ነው። አንዳንድ ሰዎች በዲፕሎማሲው መስክ ወያኔ እንደ በለጠን አርገው የሚያቀርቡ አሉ። ይኼ ጨርሶ የተሳሳተ ነው፡፡ የመንግትን ዲፕሎማሲ ስኬታማ እንዳይሆን ያደረገው ወያኔ በሚሊዮን ብር የቀጠራቸው ሎቢስቶች ናቸው እንጂ ወያኔ ራሱ በራው ራ አይደለም። ችሎታውም ስለሌለው። ወያኔ ገና ከድሮ ጀምሮ ዘለዓለም ዲፕሎማሲውን በተወሰኑ ፈረንጆች እያራ የኖረ ነው።

የሚደንቀን ግን የራሳችን መንግት ዲፕሎማሲ እንዲህ የሚፈለገውን ውጤት ሳያመጣ ሲቀር ነው። ለነገሩ የውጭ ዲፕሎማሲ እንዲራ ለማድረግ የሚፈለገው ራ በመረቱ በቀጥታ ከውጭ መንግታት ጋር ያለው በይነ ግብር ብቻ አይደለም። ዋናው ጉዳይ የአውሮፓና የአሜሪካ መንግታት ፖሊሲን ለማውጣትና ለማስፈጸም ውሳኔ ላይ የሚደርሱት እንዴት እንደሆነ ማወቁ ላይ ነው። ይህን ጥያቄ በትክክ መመለስ ዲፕሎማሲያችን የት ላይ እንደ ደከመ ለመረዳት ያስችለናል። ይህን ስንመልስ ነው በዲፕሎማሲው ረገድ በውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ (በስህተት “ዳያስፖራ” የሚባለው) ምን ያህል ወሳኝ ሚና ሊጫወት እንደሚችል መረዳት የምንችለው።

ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ በእጅጉ አብዛኛው በራሱ ጥረት ተፍጨርጭሮ የተማረና ራ የያዘ ነው። በዚህ ረገድ ያለ ምንም ማጋነን በውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ጠንካራ ራተኞች፣ በተሰማሩበት ራም ሆነ ትምህርት እጅግ የተመገኑ ናቸው። አገራቸውንም በመውደዳቸው ስለአገራቸው ዘለዓለም እንደ ተጨነቁና እንዳሰቡ ነው። የአገራቸውንም ችግር በሚመለከት ልፍ ሲጠራ እንደ ጎርፍ የሚወጡትም መዋጮም የሚያዋጡት ለአገራቸውና ለወገናቸው ባላቸው ፍቅር ነው። ብዙዎቹ አገራቸው እያሉ ያጡትን ድል በቀላሉ ሲያገኙ ወደ ትምህርት በመግባት እስከ ከፍተኛ ደረጃ ድረስ ሊማሩ ችለዋል። በአሁኑ ጊዜ በተለይም በዩናይትድ ስቴትስና ካናዳ በየዩኒቨርሲቲው በማስተማር ላይ የሚገኙት ኢትዮጵውያን ቁጥር  እጅግ ብዙ ነው። ችሎታቸውም የተመሰከረለት ነው። ከዚህ አንር ካየነው በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን ያላቸውን ምቅ ችሎታና ሙያዊ ልምድ (ኤክስፐርቲዝ) ለአገራቸው ቢያውሉት ኖሮ፣ በኢትዮጵያ ሊኖር የሚችለውን ለውጥ መገመት አይከብድም።

በአሁኑ ወቅት በተለይ ተነጥሎ ለአገራችን ኋላቀርነት ተጠያቂ የሆነው በመንግትም ሆነ በክልሉ ሴክተር ገንኖ ያለው ከፍተኛ የችሎታ ማነስ ጉዳይ ነው። በውጭ አገር ያለው የተማረው ክፍል በአገራችን ለሚያስፈልገው በኮኖሚ፣ ፖለቲካ፣ ትምህርት፣ በሕክምና፣ ወዘተ. አመራር በመስጠት ቢሳተፍ ሊገኝ የሚችለውን ውጤት በቀላሉ ማላት ይቻላል። ታዲያ በአገራችን በሚካሄደው የለውጥና የልማት ደት ውስጥ ይህን ክፍል ማሳተፍ የሚቻለው እንዴት ነው የሚለውን ጥያቄ ማንሳት ያስፈልጋል። ምን ቢደረግ ነው ይኼ አገሩን በተቻለው አቅሙ ሊረዳ የሚችለውን/የሚፈልገውን ክፍል ማሳተፍ የሚቻለው? እስካሁንስ በሚፈለገው መጠን ሊሳተፍ ያልቻለው ለምንድነው ብለን መጠየቅ ይኖርብናል።

አብዛኛው ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ ወደ ውጭ አገር በገፍ የወጣው በደርግ ጊዜ ነው። ታዲያ እንዲህ አገሩንና ወገኑን የሚወደው ኢትዮጵያዊ እንዴት ነው ደርግ ከወረደ በኋላ በአገሩ ጉዳይ በቀጥታ ሊሳተፍ ያልቻለው? መልሱ ቀላል ነው። ወያኔ የተማረ ኢትዮጵያዊ  እንደ ጦር ይፈራ ስለነበር ውጭ አገርም ያለው ኢትዮጵያዊ በነነትና በቀጥታ በፖለቲካም ሆነ በኮኖሚው እንዳይሳተፍ ለማገድ ዓላማው ስለነበር ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ አገሩ መጥቶ ከፖለቲካና መከላከያ/ጥታ በስተቀር መሳተፍ ይችላል አለ። በገ መንግቱም ውስጥ ኢትዮጵያውያን የሁለት አገር ዜግነት ሊኖራቸው አይችልም ብሎ ደነገገ። ስለዚህ ውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ተሳትፎ መብት ሳይኖራቸው፣ ወያኔ በጀመረው የከይሲዎች አገዛዝ ዝም ብለው አንገታቸውን ደፍተው እንዲሩ ደነገገ። ውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ከሁሉ አስቀድሞ የሰብዊና የሞክራሲያዊ መብት በአገራቸው እንዲኖር ይፈልጋሉ። እንዲህ ያለ መብት በሌለበት ምን ይበጀኝ ብለው ወደ አገራቸው ሊመለሱ ይችላሉ? ወያኔ ውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን በራሱ የጨዋታ ግ ተሸብበው ስለሰብዊ መብትና ስለሞክራሲያዊ መብት ሳይጠይቁ አንገታቸውን ደፍተው እንዲገዙ ፈለገ። ይ ሊሆን ስለማይችል በውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን እጅግ ብዙዎቹ ወደ አገራቸው ተመልሰው ማገልገል ቢፈልጉም ሳይመለሱ ቀሩ። ምንም ቢሆን የሚያስቡትን ሳይገላመጡ እንደ ልባቸው በሚናገሩበትና የይወት ዋስትና ባለበት በውጭ አገር ለመቆየት ወሰኑ።

ስት ዓመት በፊት የወያኔ አገዛዝ መጀመያ በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ልፍ ተደፍሮ ሲገዘገዝ ቆይቶ በኦሮሞና አማራ ወጣቶች ትግል ልጣኑን ለመልቀቅ ሲገደድና አዲስ መንግት ሲቋቋም የዝቡ ተስፋ ከፍ እንዳለው ሁሉ ውጭ አገር የሚኖረውም ኢትዮጵያዊ  ተስፋው እንደገና ብድግ አለ። የወያኔ አገዛዝ ያብቃ እንጂ ውጭ አገር አንድም ቀን ማደር የማንፈልገው ለውጡ ልባችንን ቢሰቅለውም በአንድ በኩል ደግሞ አገራችን ተመልሰን ባለን ችሎታ አገራችንን ለማገልገል ይህ ወያኔ የደነገገው ግ ካልተቀየረ ምን ያህል አስተዋጽኦ ይኖረናል የሚለው ፍርት ቀፍድዶ ያዘን። ዓይ በመጀመያው የፓርላማ ንግግራቸው ብንደመምም በተጨባጭ ግን ያ ከይሲ ግ እስካልተቀየረ ድረስ ተሳትፏችን ውሱን መሆኑ እንደማይቀር ታየን። ስለሆነም እስከ ዛሬ ድረስ እንዲህ ያለ  ጽፍ መጻፍ ከመሰለ ተሳትፎ የዘለለ ሚና ሊኖረን አልቻለም። በአንዳንድ የመንግት ባለልጣናት ዝብረቃ፣ በሚዲያ ሰዎች አሳፋሪ ድክመት፣ በአንዳንድ የክልል ባለልጣናትና ራተኞች ችሎታ ማነስ፣ በዲፕሎማሲው ድክመት እንዲሁም በሌላውም ድክመትና ስህተት ሁሉ እየተሳቀቅን መኖር ተገደናል።

ገና ያልተመለሰውና ይህንን ሁሉ ጉድ ያላየውስ ውጭ አገር ያለ ኢትዮጵያዊ  ምንም ለማድረግ የፖለቲካ መብት ከሌለው ምን ሊያደርግ ይመለስ? ይኼ ኢትዮጵያዊ  እኮ የውጭ አገር ዜግነት የወሰደው ወዶ አይደለም፣ ለይወት ዋስትና እንጂ። ከቀይ ሽብር የተረፈ፣ ከወያኔ የከይሲ አገዛዝም የተረፈው እኮ ከሁሉ አስቀድሞ የይወት ዋስትና ይፈልጋል። የውጭ አገር ዜግነት የሚሰጠው ይኼን የደንነት ዋስትና ነው። ይህ ደንነት ፖለቲካዊ ብቻ አይደለም። አንደ ሰው ራ ካጣ ለኑሮው የሚያስፈልገው ድጎማ ሁሉ ይደረግለታል። ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ እንዲህ ያለውን የደንነት ዋስትና ለምዶ የኖረ ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ የተሟላ ዋስትና እንደሌለ የታወቀ ቢሆንም የፖለቲካ ዋስትና ግን ሊኖር ይችላል። ግን የመደንገግ ጉዳይ ስለሆነ። መንግት ፖሊሲውን ማስተካከል ብቻ ነው የሚጠበቅበት። ስለሆነም ውጭ አገር የሚኖረው ኢትዮጵያዊ እንዲህ ዋስትና በሌለበት ሁኔታ ለመራት አይፈልግም። አንዳንዱም ልጆቹን ጥሎ፣ ሴቷም የምትወደውን ባሏን፣ ወንዱም የሚወዳትን ሚስቱን ትቶ ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው የደንነት ዋስትና ሁኔታ አስተማማኝ መሆን አለበት።  ከዚህም ዋናው የፖለቲካ ነነት ነው።

እንዲያው ምንም ቢሆን አገሬ ብሎ ከላይ የጠቀስነው ዋስትና ባይረጋገጥም ለውጡ ከወያኔ አገዛዝ ይሻላል ብሎ ለመመለስ ቢፈልግም አሁንም አንዳንድ እንከኖች አሉ ብሎ ስለሚያምን ተመልሶ አገሩን ለማገልገል አይቻለውም። ይህንን ለማድረግ ግን ይህ ክፍል ምን ይፈልጋል? ሰላም፣ መረጋጋት፣ የብር ፖለቲካ አምልኮ ቆሞ አገልግሎት ሰጪዎች ቀልጣፋና ትክክለኛ አራር መከተላቸው፣ ሳብን የመግለጽ ነነት ሙሉ ለሙሉ መከበር፣ የመንግት ሚዲያ አገልግሎት ለዝብ እንጂ ለመንግት አለመሆኑ፣ ወዘተ የአንድ ብር የበላይነት አለ ለሚለው ፍርቱ የማያወላዳ መልስ መስጠት፣ በተለያዩ ደረጃዎች የኮኖሚ ፕሮክቶች ሊጀምር ቢፈልግ ሊያገኝ ስለሚችለው የመንግት ትብብር ርግጠኛ አለመሆን፣ ወዘተ. አገር አደጋ ላይ ስትሆን ያሳየው መተባበር ያሉትን ጥርጣሬዎችና ጥያቄዎች አስወግዷል ማለት አይደለም። “ዳያስፖራው” በዲፕሎማሲው ሊካፈል ይገባል እየተባለ ስለ“ዳያስፖራው” የፖለቲካ መብት ግን ምንም አለመነሳቱ ዋና እንቅፋት ሆኖበታል። ስለሆነም ከሁሉ በፊት ፖለቲካዊ መልስ ይፈልጋል።

ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ ለገሪቱ ዲፕሎማሲያዊ ስኬት ያለው አቅም ከፍተኛ ነው። እንደ አውሮፓዊ ወይም አሜሪካዊ ዜጋ ያለው የዜግነት መብት ፍተኛ ስለሆነ ያለበት አገር መንግት የሚከተለውን የውጭ ፖሊሲ የመጠየቅ ሲልም የመቃወም መብቱ የተጠበቀ ከመሆኑም በላይ በፓርላማ ባልተወሰኑ ግን መንግት በራሱ በሚወስዳቸው ፖሊሲዎች አንድ ዜጋ የፓርላማ አባላትንና ሌሎች ፖለቲከኞችን እየነዘነዘ ለሚዲያም መረጃ እየሰጠ ፖሊሲው እንዲቀየር ወይም እንዳይሳካ ማድረግ ይችላል። ይኼ እንግዲህ በግለሰብ ደረጃ አንድ ሰው ሊያደርገው የሚችለው ነው። እዚህ ላይ ደግሞ መደራጀትና መቀናጀት ሲታከልበት ውጤቱም ይበልጥ ስኬት ሊያሳይ ይችላል።

ቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው ስለዲፕሎማሲው ካነሱት ጉዳይ አንዱ ኤምባሲዎችን የመቀነስና ውጭ ያለውን ኢትዮጵያዊ ትብብር መሻት ያሉት ጥሩ ሳብ ነው። ቢሆንም ውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ቢደረግለት ስለሚፈልገው ደግሞ ግልጽ መሆን ያስፈልጋል። መብትና ነነትን ያላዘለ ጥሪ የደርጉን “የእናት አገር ጥሪ” እንዳይመስል መጠንቀቅ ያስፈልጋል። ኤምባሲ መቀነስ ሳቡ ጥሩ ቢሆንም ሊያስከትል የሚችለውን የአሠራር ምስቅልቅል በቅጡ አጢኖ መዘጋጀትን ይጠይቃል። ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ ከኤምባሲው ራ ሊሸፍን የሚችለው ውትወታና ማግባባቱን (አድቮኬሲና ሎቢውን) ብቻ ይመስለኛል። ሌሎች ክኖትራክቹዋል የሆኑ ጉዳዮችን ሊሸፍን አይችልም። ይህን የመሳሰሉት ራዎች እንዴት እንደሚሩ በቅጡ መጤን አለበት። በርግጥ እንደ ቪዛ ያሉት ጉዳዮች ከአስ አበባ ሆኖ በኦንላይን ሊሩ ይችላሉ። ሌሎች በኦንላይን ሊሩ የማይችሉ ጉዳዮች እንዳሉም የታወቀ ነው። የሆነው ሆኖ ግን ውጭ አገር ያለው ኢትዮጵያዊ በአድቮኬሲና ሎቢ ብዙ አስተዋጽኦ ያደግ ይችላል። ከሁሉ አስቀድሞ ግን የሚገባውን የፖለቲካ መብቱን ማክበር ያስፈልጋል። ውጭ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵያያን ሁለት ዓይነት ዜግነት ሊኖራቸው እንደሚችልና በፖለቲካውም ለመሳተፍ እንደሚችሉ በግ መደንገግ አለበት።

ርግጥ የሁለት አገር ዜግነት ጉዳይ በኢትዮጵያ መንግት ብቻ የሚወሰን ሳይሆን የሌሎቹንም አገሮች ግ የሚመለከት ነው። በሽብርተኞች ምክንያት አንዳንድ አገሮች የሁለት አገር ዜጋነት የሚለውን በግ ሰርዘዋል። እንዲህ ባለው ሁኔታ ውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን በአገራቸው የፖለቲካ ደት ውስጥ የመሳተፍ መብታቸው ግን ሊደነገግ ይችላል። በኢትዮጵያ የፖለቲካ ደት ውስጥ ወደ ሞክራሲ በሚደረገው ሽግግር፣ ብሎም በኮኖሚውም፣ በትምህርትና በሕክምና ረድፍ በመሳተፍ ውጭ አገር ያሉ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ሊያደርጉ ይችላሉ፡፡ የፖለቲካ መብታቸው ከታወቀና ከላይ የጠቀስናቸው የፖለቲካና የአሠራር እንቅፋቶች ከተነሱ ማለት ነው

ከአዘጋጁጽሑፉ የጸሐፊውን አመለካከት ብቻ የሚያንፀባርቅ መሆኑን እየገለጽን፣ በኢሜይል አድራሻቸው [email protected] ማግኘት ይቻላል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...