Friday, September 22, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናበአፋር ክልል በቀጠለው ጦርነት ሳቢያ ወደ ትግራይ ሰብዓዊ ዕርዳታ ማቅረብ አለመቻሉን የዓለም...

በአፋር ክልል በቀጠለው ጦርነት ሳቢያ ወደ ትግራይ ሰብዓዊ ዕርዳታ ማቅረብ አለመቻሉን የዓለም ምግብ ድርጅት ገለጸ

ቀን:

በአፋር ክልል በቀጠለው ጦርነት ምክንያት ምግብና ሌሎች ሰብዓዊ ዕርዳታዎችን ወደ ትግራይ ለማድረስ መቸገሩን የዓለም የምግብ ድርጅት ገለጸ፡፡

የዓለም የምግብ ድርጅት ዋና ኃላፊ ዴቪድ ቤስሌይ ይፋ እንዳደረጉት፣ ወደ ትግራይ ክልል ምክብና ሌሎች የሰብዓዊ ዕርዳታ ቁሶችን የጫኑ 170 ተሽከርካሪዎች አፋርን ማለፍ ተቸግረው ቆመዋል፡፡

የዓለም የምግብ ድርጅት በትግራይ ክልል ውስጥ ባሉት መጋዘኖች የተከማቸ የምግብ ዕርዳታ ከመጪው ከዓርብ ሐምሌ 23 ቀን 2013 ዓ.ም. በኋላ ባዶ እንደሚሆን ገልጸው፣ ‹‹በአፋር ጦርነት ምክንያት ለመቆም የተገደዱት ተሽከርካሪዎች በአስቸኳይ እንዲያልፉ ሊደረግ ይገባል፣ ሰዎች እየተራቡ ናቸው፤›› ሲሉ ጥሪ አድርገዋል፡፡

መንግሥት ማክሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2013 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው መረጃ፣ ለሰብዓዊ ዕርዳታ ሲል የወሰነው የተናጠል የተኩስ አቁም በሕወሓት ትንኮሳ ክልል እየገጠመው እንደሆነ አስታውቋል፡፡

ከተኩስ አቁም ውሳኔው ባለፈ መንግሥት በትግራይ በሚገኙ መጋዘኖች አራት መቶ ሺሕ ኩንታል ስንዴና 2.5 ሚሊዮን ሊትር የምግብ ዘይት ተደራሽ እንዲሆን ማድረጉንም ጠቁሟል፡፡

‹‹በትግራይ የሚገኙ ዜጎቻችን ደኅንነት ያሳስበናል›› ያለው መግለጫው፣ ዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ በተለይም በትግራይ ክልል የሚንቀሳቀሱ ዓለም አቀፍ ተቋማት ሕወሓት በአፋር በኩል የሚያደርገውን ትንኮሳ እንዲያቆም ግፊት ሊያደርጉ ይገባል ሲል ጥሪውን አቅርቧል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ባለሙያዎች ኮሚሽን ሪፖርት ምን ይዟል?

ለአሜሪካ ድምፅ አማርኛ ዝግጅት የስልክ አስተያየት የሰጡ አንድ የደንበጫ...

መንግሥት በአማራ ክልል ለወደሙ የአበባ እርሻዎች ድጋፍ እንዲያደርግ ተጠየቀ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአማራ ክልል የተፈጠረው ግጭትና አለመረጋጋት በቢዝነስ...

አምናና ዘንድሮ!

እነሆ መስከረም ጠብቶ በአዲስ መንፈስ ተሞልተን መንገድ ጀምረናል። ‹‹አዲስ...