Friday, December 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየቀድሞ ኤታማዦር ሹም ፃድቃን ገብረ ትንሳዔና እነ ጀነራል ታደሰ ወረደ ...

የቀድሞ ኤታማዦር ሹም ፃድቃን ገብረ ትንሳዔና እነ ጀነራል ታደሰ ወረደ ሜጀር ጀነራል ዮሐንስ ወልደጊዮርጊስ ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ መኮንኖች ላይ ክስ ተመሰረተ

ቀን:

የፌደራል ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ  ከህውሐት ቡድን  ጋር  ተሳትፎ አላቸው ያላቸውን የቀድሞ ኤታማዦር ሹም ጀነራል ፃድቃን ገብረ ትንሳዔና እነ ሌተናል ጀነራል ታደሰ ወረደ፣ ዮሐንስ ወልደ ጊዮርጊስን ጨምሮ በ74 ከፍተኛ መኮንኖችና  ግለሰቦች የሽብር ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው፡፡

የሽብር ወንጀል ክሱ የተመሰረተባቸው ከፍተኛ  መኮንኖች መካከል ሌተናል ጄነራል ታደሰ ወረደ ፣ሜጀር ጀነራል ዩሀንስ ወልደጊዮርጊስ፣ ብርጋዴር ጄነራል ምግባይ ሀይለ፣ሜጀር ጀነራል ሀለፎም አለሙ፣ ሜጀር ጀነራል ሀለፎም እጅጉ፣ ሜጀር ጄነራል አታክልቲ በርሄና ሜጀር ጀነራል ማሾ በየነ ይገኙበታል። አቶ ሀዱሽ አበበና አቶ ቢኒያም ተወልደም በክሱ ተካተዋል።

ተከሳሾቹ ከህውሐት አመራሮች ተልኮ ተቀብለው ወታደራዊ  ኮማንድ  በማደራጀትና በመምራት፣ በፌደራል ፖሊስ፡  በሰሜን ዕዝ ጦር፣የአማራና የአፋር ክልሎች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን ዓቃቤ ህግ  በክሱ ተካቷል።

ክሱ በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የፀረ ሽብርና የህገመንግስት ጉዳዮች ወንጀል ችሎት የተመሰረተ ቢሆንም  ቢሆኑም ዳኞች ባለመሟላታቸው ምክንያት የመጥሪያ ቀጠሮ  አልተሰጠም፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...