Monday, March 20, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየጎርፍ አደጋ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ

የጎርፍ አደጋ በሰውና በንብረት ላይ ጉዳት አደረሰ

ቀን:

ትናንት ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም.  ከሰዓት በአዲስ አበባ ከተማ የጣለው በረዶ የቀላቀለ ከባድ ዝናብ ምክንያት በተለያዩ የከተማዋ አካባቢዎች የጎርፍ አደጋ ተከስቶ በሰው ሕይወትና ንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡

በአስኮ፣ በአደይ አበባ፣ በጀርመን አደባባይና በጎልፍ ክለብ አካባቢ በደረሰው ከፍተኛ የጎርፍ አደጋ መንገዶች ጭምር ተዘጋግተው ቆይተዋል፡፡ የድንገተኛና የእሳት አደጋ ሠራተኞችም በቦታዎቹ በመገኘት የከፋ ሰብዓዊ ጉዳት እንዳይደርስ ከፍተኛ ጥረት በማድረጋቸውን ምክትል ከንቲባ አዳነች አበቤ በይፋዊ የፌስቡክ ገጻቸው ገልጸዋል፡፡ ‹‹በደረሰው ጉዳት ከልቤ አዝናለሁ፤›› ብለዋል።

ተጎጂዎችንም ወደክምና መስጫ በማጓጓዝና የመጀመርያክምናርዳታ እንዲያገኙ መደረጉንም ተናግረዋል፡፡ የከተማው አስተዳደር ከክረምቱ ማየል ጋር ተያይዞ አስቀድሞ የመከላከልራዎችን እየሠራ የነበረ ቢሆንም፣ ትናንትና ነሐሴ 11 ቀን 2013 ዓ.ም. የደረሰው የጎርፍ አደጋ ተጨማሪ ሥራዎችን መሥራት እንደሚገባ ያመላከተ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡  መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በመጪዎቹ ቀናት ከፍተኛ መጠን ያለው የዝናብ ሥርጭት ስለሚኖር ነዋሪዎች አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉ አሳስበዋል

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ዜጎች የተፈተኑበት የኑሮ ውድነት

በኢትዮጵያ በየጊዜው እየተባባሰ የመጣው የኑሮ ውድነት የበርካታ ዜጎችን አቅም...

በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎች ዘላቂነት እንዲኖራቸው ተጠየቀ

በድርቅ ለተጎዱ አካባቢዎች የሚደረጉ ድጋፎች ዘላቂነት እንዲኖራቸውና በተቀናጀ መልኩ...

ወደ ኋላ የቀረው የሠራተኞች ደኅንነት አጠባበቅ

በአበበ ፍቅር ለሠራተኞች የሚሰጠው የደኅንነት ትኩረት አናሳ በመሆኑ በርካታ ዜጎች...