Sunday, March 26, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየ53 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሴት አባላት የጋራ ምክር ቤት መሠረቱ

የ53 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሴት አባላት የጋራ ምክር ቤት መሠረቱ

ቀን:

በኢትዮጵያ የሴቶችን የፖለቲካ ተሳትፎ ለማሳደግ በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ 53 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሴት አባላት የጋራ ምክር ቤት መሠረቱ፡፡

በብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሴቶች የጋራ ምክር ቤት የመሠረቱት ዓርብ ነሐሴ 28 ቀን 2013 ዓ.ም. ሲሆን፣ የምክር ቤቱ መመሥረት ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎችና ደጋፊዎቻቸው በሴቶች የፖለቲካ ተሳትፎ ላይ እንዲሠሩ እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።

የጋራ ምክር ቤቱ መሥራችና ሥራ አስፈጻሚ አባል ነቢሐ መሐመድ እንደተናገሩት፣ በቅርቡ በተካሄደው ስድስተኛው አገር አቀፍ ምርጫ ላይ በዕጩነት ከቀረቡ 9,505 ተወዳዳሪዎች መካከል የሴቶች ቁጥር 1,987 ብቻ ነው።

ይህ አኃዝ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሴት ዕጩ ተወዳዳሪዎችን በማቅረብ ረገድ ሰፊ ክፍተት እንዳለባቸው የሚያመላክት መሆኑን ገልጸዋል። በመሆኑም የሴቶችን የፖለቲካ መስክ ተሳትፎና አመራር ሰጪነት ለማሳደግ ሁለንተናዊ ጥረት የሚያስፈልግ በመሆኑ፣ የጋራ ምክር ቤቱ መመሥረቱ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አስረድተዋል፡፡

ፓርቲዎች አባላት ሲመለምሉ ሴት ዕጩዎችን በሥራ አስፈጻሚነት የኃላፊነትርከን የማምጣት ተግባራትን ማከናወን እንደሚጠበቅባቸው ጠቁመው፣ የጋራ ምክር ቤቱ ሴቶች በተለይም በፖለቲካው መስክ ተሳትፏቸው የሚያጋጥሙ ችግሮችን በጋራመታገል የሚያስችል ዕድል እንደሚከፍትላቸው ያላቸውን እምነት አውስተዋል።

በምክር ቤቱ በአባልነትም ይሁን በሌሎች መስኮች መሳተፍ የሚችሉት በአገሪቱ ሕጋዊ ምዝገባ አካሂደው የሚንቀሳቀሱ 53 የፖለቲካ ፓርቲዎች ሴት አባላት ብቻ መሆናቸውንም አስታውቀዋል።

የጋራ ምክር ቤቱ በአገሪቱ በሕጋዊነት ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሴት አባላት በግለሰብ ደረጃ የሚሳተፉበትና በፖለቲካው መድረክ እጅግ አነስተኛ የሆነውን የሴቶች ተሳትፎን ክፍተት ለመሙላት ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት፣ በምሥረታው ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ውብሸት አየለ ተናግረዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ለፋይናንስ ዘርፉ ብቃት ያለው የሰው ኃይል የማፍራት የቤት ሥራን የማቃለል ጅማሮ

የአገሪቱ የፋይናንስ ዘርፍ እያደገ ለመሆኑ ከሚቀርቡ ማስረጃዎች ውስጥ  የግል...

የምድር ባቡርን የሚያነቃቃው የመንግሥት ውሳኔ

በኢትዮጵያ ወደብ አልባነት ላይ የተደመረውን የሎጀስቲክስ ችግር ለመፍታት ግዙፍ...

የፓርላማ አባላት ስለሰላም ስምምነቱ አፈጻጸም ግልጽ መረጃ የለንም አሉ

‹‹ሕወሓትን ለፍረጃ አብቅተውት የነበሩ ጉዳዮች በአብዛኛው መልክ ይዘዋል›› ሬድዋን...