Wednesday, March 22, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ አዲሱን ዓመት ለመቀበል የተዘጋጁ ክብረ በዓላትን በተመለከተ ከአዘጋጅ ኮሚቴው ሰብሳቢ ጋር በስልክ እየተወያዩ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር አዲሱን ዓመት ለመቀበል በአምስቱም የጳጉሜን ወር ቀናት ዝክሮች አዘጋጅተን ለሕዝብ ይፋ ተደርገዋል፣ ሚዲያዎችም እያስተዋወቁ ናቸው።
  • እኔም የደወልኩት የክብረ በዓላቱን ዝርዝር ተመልክቼ ነው፡፡
  • በአምስቱም ዝክረ ቀናት የተዘጋጁትን ፕሮግራሞች እንዴት አገኟቸው ታዲያ ክቡር ሚኒስትር?
  • የምን ዝክር ነው የምታወራው? ጥሩ አገላለጽ አይደለም። 
  • እሺ፣ ይስተካከላል ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • መስተካከል አለበት፣ ዝክር ምናምን ማለቱን ተውና አዲሱን ዓመት ለመቀበል የተዘጋጁ ቀናት ይባሉ፡፡
  • ቀናት? 
  • ታዲያ ምን ይሻላል? በዓላት ይባሉ እንዴ?
  • በዓል አላዘጋጀንማ ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • ታዲያ ምን ይሻላል? 
  • ክቡር ሚኒስትር ፕሮግራሞቹ ኢትዮጵያዊነትን፣ አገልጋይነትን ለመቀስቀስ በመሆናቸው ዝክረ ቀናት ቢባሉ ይሻላል፣ ኢትዮጵያን መዘከር እንደ ማለት ነው።
  • ብቻ ቃሉን አልወደድኩትም፣ ሌላ የሚመጥን ከሌለ ምን ይደረጋል? ግን ጥንቃቄ አድርጉ፡፡ 
  • የምን ጥንቃቄ?
  • እንዘክራለን ብላችሁ መድረኩ ሌላ የፖለቲካ አታካራ መቀስቀሻ እንዳይሆን፡፡ 
  • ተሳታፊዎችን በጥንቃቄ ነው የመረጥነው፣ አያስቡ ክቡር ሚኒስትር። 
  • ሌላም መስተካከል ያለበት ነገር አለ፣ መስተካከል ብቻ ሳይሆን ማብራሪያም እፈልጋለሁ።
  • ምንድነው ጉዳዩ? ይንገሩኝ ማብራሪያ እሰጥበታለሁ ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • አዎ ማብራሪያ ያስፈልገዋል፣ አልያም መሰረዝ አለበት።
  • ምኑ?
  • የመጨረሻው ቀን ላይ ይከናወናል ያላችሁት ነገር። 
  • እ… በመጨረሻው ቀን ያሰብነው የድል …
  • እንዴት ነው በዚህ ተለዋዋጭ ሁኔታ ውስጥ ድል ይበሰራል የምትሉት? እንዴት ነው እርግጠኛ የሆናችሁት?
  • ሥጋትዎ ገብቶኛል ክቡር ሚኒስትር፡፡ 
  • ቢገባህ ነው እንዲህ ዓይነት መንግሥትን አጣብቂኝ ውስጥ የሚከት ዝግጅት የምታሰናዳው?
  • በጥንቃቄ ነው እኮ ፕሮግራሙን ያሰናዳነው ክቡር ሚኒስትር። 
  • እኮ አብራራልኛ? እንዴት ተደርጎ በአንድ ሳምንት ሁሉ ነገር እንደሚያልቅና ድል እንደሚበሰር አብራራልኝ፡፡
  • በዕለቱ የሚበሰር ድል የሚኖር ከሆነ ብቻ ነው ድሉ የሚበሰረው። 
  • ምን ማለት ነው? ድል የሚበሰርበት ቀን ብለህ ድሉ አልደረሰም ብለህ ልታበስር ነው?
  • ክቡር ሚኒስትር እንደዚያ አይደለም። 
  • እና እንዴት ነው?
  • ቃሉን በጥንቃቄ ነው የቀረፅነው ያልኩት ለዚህ ነበር።
  • ምንድነው በጥንቃቄ ማለት?
  • ለዕለቱ ዝግጅት የመረጥነው ቃል ድል የሚል ቃል ይኑረው እንጂ በዕለቱ ድል ይኖራል ማለት አይደለም፣ በጥንቃቄ ነው የሰየምነው ያልኩት ለዚያ ነው።
  • ምንድነው ስያሜው? የድል ብሥራት ቀን አይደለም እንዴ የሚለው?
  • አይለም ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ምንድን ነው ያላችሁት ታዲያ?
  • የድል ቃል ኪዳን ብሥራት ቀን ነው ያልነው።
  • ምን ማለት ነው ደግሞ እሱ?
  • ድል ከተገኘ ድሉ ይበሰራል። 
  • ድል ከሌለ ምን ልታደርጉ ነው?
  • ከሌለ ደግሞ ድል ለማድረግ ቃል ኪዳን የምንገባበት ይሆናል።
  • ጥሩ ዘዴ ነው የቀየሳችሁት።
  • በጥንቃቄ ነው የመረጥነው ያልኩት ለዚህ ነው ክቡር ሚኒስትር፡፡
  • ግልጽ ሆኖልኛል አሁን፣ ለማንኛውም ጥንቃቄ ይደረግ።

[የክቡር ሚኒስትሩ የእጅ ስልክ ጠራ፣ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ሆነው የተመደቡት አምባሳደር ናቸው የደወሉት]

  • እንደምን አሉ አምባሳደር?
  • የተጣበበ ሁኔታ ውስጥ ሆነው እኔን ለማነጋገር ስለፈቀዱ አመሰግናለሁ ክቡር ሚኒስትር። 
  • ምንም አይደል፣ አመሠግናለሁ፡፡ 
  • ክቡር ሚኒስትር ድርድር እንዲመቻች በመጠየቅ ለዓለም መንግሥታት የተሠራጨውን ደብዳቤ በተመለከተ በእናንተ በኩል የተያዘውን አቋም ለመረዳት ነው የደወልኩት።
  • በእኛ በኩል ሰላም ነው የምንፈልገው፣ ሌላ አቋም የለንም።
  • እኮ ወደዚያ ለመምጣት በእነሱ በኩል ድርድር እንዲካሄድ ነው የጠየቁት፣ በእናንተ በኩል ለድርድር ዝግጁነት አለ?
  • እኛ ወደ ውጊያ ከመግባታችን በፊት ጀምሮ ችግሩ በሰላም እንዲፈታ ከመጠየቅ አልፈን ለምነናል።
  • እሱን አውቃለው፣ አሁን ዝግጁ መሆናችሁን ነው ለመረዳት የፈለግኩት?
  • አሁንም ነገም ዝግጁ ነን በእኛ በኩል፣ ነገር ግን ያልተረዳነው ነገር አለ።
  • ምንድነው ያልተረዳችሁት?
  • ከማን ጋር እንደምንደራደር፡፡
  • እንዴት? በእነሱ በኩል እኮ ጥያቄው ቀርቧል፡፡
  • ገባኝ፣ ግን ከማን ጋር እንደምንደራደር ማወቅ እንፈልጋለን፡፡
  • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር? 
  • የሚደራደረው የትኛው አካል ነው?
  • አመራሩ ነዋ ክቡር ሚኒስትር?
  • የተፈረጀው ነው ወይስ ያልተፈረጀው?
  • እሱን አልገለጹም።
  • ሲገልጹ ብንወያይ አይሻልም?

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና የመንግሥት ውዝግብ

የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) መንግሥት ባለፉት አራት ዓመታት...

የኢትዮጵያ ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት ሥጋቶች

ዘ ኮንቨርሴሽን ላይ ‹‹What Next for Ethiopia and its...

 የክልሎች ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በመከላከያ ሠራዊት ተጠባባቂ ኃይል እንዲካተቱ ጥናት እየተደረገ ነው

የክልሎችን ልዩ ኃይልና ሚሊሻ በአገር መከላከያ ሠራዊት ተጠባባቂ ኃይል...

ኢትዮጵያ በትክክለኛ ግንዛቤ ላይ የተመሠረተ ሕገ መንግሥት ማበጀት እንደሚገባት ማሳሰቢያ ተሰጠ

የኢትዮጵያ ሕገ መንግሥት ከተረቀቀበት ጊዜ አንስቶ ለተለያዩ ጥያቄዎችና ሐሳቦች...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...

ዘምዘም ባንክ ለሴቶችና ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች የፋይናንስ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አስታወቀ

ሙሉ በሙሉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎትን በማስተዋወቅ ቀዳሚ የሆነው...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...