Thursday, November 30, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናኢትዮጵያ በፍቅር የሚቀርቧትን አገሮች በፍቅር እንደምትቀበል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ኢትዮጵያ በፍቅር የሚቀርቧትን አገሮች በፍቅር እንደምትቀበል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናገሩ

ቀን:

የፖለቲካ ልዩነቶችን ለማጥበብ አካታች ብሔራዊ የውይይት መድረክ እንደሚካሄድ አስታወቁ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (/) በአዲሱ መንግሥት ምሥረታና በበዓለ ሲመታቸው ላይ ለተገኙ፣ የአፍሪካ አገሮች መሪዎችና የተያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በተገኙበትነ ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግርኢትዮጵያ በፍቅር የሚቀርቧትን ወዳጅ አገሮችን በበጎ እንደምትቀበል አስታወቁ። 

በኢትዮጵያም ሆነ በሌሎች የፓርላማ ፖለቲካ ሥነ ሥርዓትን በሚከተሉ አገሮች ባልተለመደ መንገድ በተካሄደው የጠቅላይ ሚኒስትርብይ በዓ ሲመት ላይ፣ የምዕራብ አፍሪካና የምሥራቅ አፍሪካ አገሮችን የሚወክሉ የአገር መሪዎች ታድመዋል።

ሰኔ 14 ቀን 2013 ዓ.ም. በተካሄደው አጠቃላይ ምርጫ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትን አብላጫ ወንበር ያሸነፈው ብልፅግና ፓርቲ፣ የፓርቲውን ሊቀመንበር በጠቅላይ ሚኒስትርነት እንዲያገለግሉ በመምረጡ፣ ይህንኑም ሰኞ መስከረም 24 ቀን 2014 ዓ.ም. ማለዳ ለተሰበሰበው ምክር ቤት ማሳወቁን ተከትሎ፣ ምክር ቤቱፓርቲውን ውሳኔ ተቀብሎ ሊቀመንበሩንብይ አህመድ (/) በጠቅላይ ሚኒስትርነት ሰይሟል።

የምክር ቤቱርዓት ተጠናቆ ካበቃ ከቀትር በኋላ የጠቅላይ ሚኒስትሩ በዓ ሲመት በመስቀል አደባባይ የተከበረ ሲሆን፣ በዚህም ወቅት በእንግድነት የተጋበዙት የአፍሪካ አገሮች መሪዎች ንግግር በማድረግ ከጠቅላይ ሚኒስትርብይ (ዶ/ር) መንግሥትና የአፍሪካ ተምሳሌት ከሆነች ኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ጋር አብረው እንደሚሠሩ አረጋግጠዋል።

መሪዎቹ በተከታታይ ንግግር አድርገው ካጠናቀቁ በኋላ፣ ጠቅላይ ሚኒስትርብይ (ዶ/ር) በመድረኩ ለተገኙ እንግዶችና ለመላው የኢትዮጵያዝብ ንግግር አድርገዋል።

ንግግራቸውን ባደረጉበት ወቅትም ኢትዮጵያ የገጠማትን የውስጥ ቀውስ ተከትሎ የበረታባትን የውጭ ጫና በመቃረን፣ ከኢትዮጵያ ጎን ለቆሙ አገሮች ምሥጋና አቅርበዋል። 

አክለውም ኢትዮጵያን ለመጫን የሞከሩና የሚሞክሩ አገሮችን በተመለከተ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

‹‹ኢትዮጵያ ወደ ብልፅግና ለምታደርገው ጉዞ የወዳጆቿን ድጋፍ ትሻለች። ነገር ግን ማንኛውም ወዳጅነት የኢትዮጵያን ክብርና ሉዓላዊነት በሚሰዋ መልኩ መሆን የለበትም፣ ሊሆንም አይችልም፤›› ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚሁ ጉዳይ ላይ አክለው ሲናገሩም፣ ‹‹በፍቅር መንፈስ ለሚቀርቡን አገሮች ልባችንና በራችን ለድጋፋቸውና ለምክራቸው ሁሌም ክፍት ነው፤›› ብለዋል።

ኢትዮጵያ የገጠማትን የውስጥ ችግር እንደምትፈታ ያረጋገጡት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ችግሮቹን ለመፍታትም በአጭር ጊዜ ውስጥ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይት መድረክ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።

‹‹የፖለቲካ ልዩነቶቻችንን ለማጥበብ አካታች ብሔራዊ የውይይት መድረክ እናካሂዳለን፤›› ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ የሚካሄደው ውይይት በኢትዮጵያውያን እንደሚመራና የኢትዮጵያ ወዳጅ አገሮች ደግሞ በዚህ ውስጥ ሚና እንደሚኖራቸው ገልጸዋል።

‹‹ችግሮቻቸውን ተመካክረው ይፈታሉ ብለው የሚያምኑብንን ያካተተና በኢትዮጵያውያን የሚመራ ሁሉን አቀፍ የውይይት መድረክ እናካሂዳለን፤›› ሲሉ አገረጋግጠዋል።

ይህ የጠቅላይ ሚኒስትሩ መልዕክት በማለዳው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና የፌዴሬሽን ምክር ቤት የጋራ ስብሰባ ወቅት፣ በፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የመክፈቻ ንግግር ላይም በግልጽ ተንፀባርቆ ነበር።

‹‹የገጠሙንን ሰንኮፎች በብሔራዊ ውይይት መፍታት ይኖርብናል፤›› ያሉት ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ፣ ብሔራዊ ውይይት የረዥም ጊዜደትን የሚጠይቅ እንደሆነና መግባባት ላይ ለመድረስም ትዕግሥትን እንደሚጠይቅ ገልጸዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...