Sunday, April 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዝንቅ‹‹ደመናውም ሸሸ እያጉረመረመ››

‹‹ደመናውም ሸሸ እያጉረመረመ››

ቀን:

መስከረም ‹‹ከረመ›› ከሚለው ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጓሜውም ቀዳማይ፣ ለዓለም ሁሉ መጀመሪያ፣ ርእሰ ክራማት፣ መቅድመ አውራኅ ማለት ነው፡፡ መስከረም፣ ዐውደ ዓመት፣ የክረምት ጫፍ መካተቻ፣ የመፀው መባቻ ማለትም ይሆናል፡፡ መስከረም ከጥንት ጊዜ ጀምሮ ለዓለም ሁሉ የመጀመሪያ ወር እንደሆነ ይታመንበታል፡፡

መስከረም በክረምት ውስጥ የሚካተት ቢሆንም የጨለማው ጊዜ አልፎ ብርሃን የሚታይበት፣ ዕፀዋትና አዝርዕት የሚያብቡበትና የሚያፈሩበት፣ እንስሳት የጠራ ውኃ እየጠጡ፣ ለምለም ሣር እየነጩ የሚቦርቁበት፣ በአጠቃላይ ምድር በአበቦች የምታጌጥበት፣ ሰማይ የደመና ቡሉኮውን (ጋቢውን) ጥሎ ቀን ብቻ ሳይሆን ሌሊት በከዋክብት ማጌጥ የሚጀምርበት ወቅት በመሆኑ ልዩ ወር ናት፡፡ ለዚህም ነው በሰኔ መጨረሻ፡-

‹‹ነው ወይ ልንለያይ ልንበታተን
      ዳግመኛ ለመምጣት ተስፋ ሳይኖረን፤››
እያለ በእንባ የተለያየው ተማሪ በመስከረም ወር ተመልሶ ትምህርት ቤት ሲገናኝ፡-
‹‹መስከረም መስከረም መስከረም ለምለም
ከወራቱ ሁሉ እንደ አንቺ የለም
ደመናውም ሸሸ እያጉረመረመ
በመስከረም ማማር እየተገረመ፤››
በማለት የሚዘምረው፡፡

– ካሕሣይ /እግዚአብሔር ‹‹ኅብረብዕር›› (1998)

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ኦቲዝምን ለመቋቋም በጥምረት የቆሙት ማዕከላት

ከኦቲዝም ጋር የሚወለዱ ልጆች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ...

አወዛጋቢው የወልቃይት ጉዳይ

የአማራና ትግራይ ክልሎችን እያወዛገበ ያለው የወልቃይት ጉዳይ ዳግም እየተነሳ...

ተጠባቂው የቴሌኮም ኦፕሬተሮች የውድድር መለኪያ የሆነው የሞባይል ገንዘብ ዝውውር በኢትዮጵያ

የሞባይል ገንዘብ ዝውውር የሞባይል ስልክን በመጠቀም ሊገኙ የሚችሉ የፋይናንስ...

የአማራና ደቡብ ክልሎች ለሠራተኛ ደመወዝ መክፈል መቸገራቸውን የፓርላማ አባላት ተናገሩ

በአማራና በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልሎች የሚገኙ የመንግሥት ተቋማት...