ሙሴ ባህር ከፍሎ ሕዝቡን አሻገረ፣
በታላቁ መጽሐፍ ይኼ ቃል ነበረ፤
የእኛ ሙሴ መርቶን፣
የአርነትን መንገድ በሩቅ አመላክቶን፣
በበረሃ ጉዞ ወንዙ ፊት አድርሶን፤
ይከፍለዋል ስንል ባህሩን በእጆቹ፣
መርከቡን ተሳፍሮ ከእነዘመዶቹ፣
በተስፋ ስናየው እንሳፈር ብለን፣
‹‹ዋና የምትችሉ ተከተሉኝ!›› አለን፡፡
ከነዓን ምድር ላይ ያሰበው ቢሞላም፣
ሙሴ ሕዝቡን መርቶ እሱ ግን አልገባም፤
እኛ መሪ ብለን ታምነነው ወጥተናል፣
እሱ እስራኤል ገብቶ እኛ ግን ቀርተናል፡፡
- ሰሎሞን ሞገስ ‹‹የተገለጡ ዓይኖች›› (2009)