Thursday, December 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናኦፌኮ በብሔራዊ ውይይት ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀመጠ

ኦፌኮ በብሔራዊ ውይይት ለመሳተፍ ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀመጠ

ቀን:

መንግስት አካሂዳለሁ ባለው ብሔራዊ ውይይት ለመሳተፍ አራት ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጡን የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) አስታወቀ።

መንግስት ለማካሄድ ያቀደው ብሔራዊ ውይይት የዘገየ ቢሆንም ተቀባይነት ያለው መሆኑን የገለጸው ኦፌኮ ፤
ብሔራዊ ውይይቱ ከመካሄዱ አስቀድሞ ግን መሟላት አለባቸው ያላቸውን ቅደመሁኔታዎች አስቀምጧል።

ካስቀመጣቸው ቅድመ ሁኔታዎች መካከልም ፤ በሕግ ማስከበር ስም ተጀምሮ የሕልውና ማስጠበቅ ዘመቻ የተለባለው ጦርነት በሁሉም አቅጣጫ በአስቸኳይ ቆሞ ሁሉን አቀፍ ብሔራዊ ውይይቱ እንዲደረግ፣ ብሔራዊ ውይይቱ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብና በሁሉም ተሳታፊ ወገኖች ተቀባይነት ባላቸው ገለልተኛና ተዓማኒ አካላት እንዲመራ የሚሉት ይገኙበታል።

በተጨማሪም ፤ ብሔራዊ ውይይቱ የታጠቁ ተቃዋሚ ቡድኖችን ጨምሮ ሁሉንም የፖለቲካ ቡድኖች ያካተተ እንዲሆን ፤ የእነዚህን ቡድኖች ውክልና ለማንቃትም የሕጋና የደህንነት መሰናክሎች ከወዲሁ እንዲወገዱ እና የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ተፈትተው በውይይቱ እንዲሳተፉ እንዲፈቀድ ሲል ኦፌኮ ቅድመ ሁኔታዎችን ማስቀመጡን በመግለጫው አስታውቋል። ኦፌኮ በመረራ ጉዲና (ፕሮፌሰር) እንደሚመራ ይታወቃል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...