Monday, October 2, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየተፎካካሪ ፓርቲዎች አባላትና ደጋፊዎች ከፀጥታ ኃይሉ ጎን እንዲሰለፉ ጥሪ ቀረበ

የተፎካካሪ ፓርቲዎች አባላትና ደጋፊዎች ከፀጥታ ኃይሉ ጎን እንዲሰለፉ ጥሪ ቀረበ

ቀን:

የፓለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ የተፎካካሪ ፓርቲዎች አባላትና ደጋፊዎች አሁን ባለው አገራዊ ሁኔታ ከፀጥታ ኃይሉ ጎን እንዲሰለፉ ጥሪ አቀረበ።

ምክር ቤቱ ጥሪውን ያቀረበው ዛሬ ጥቅምት 27 ቀን 2014 ዓም በካፒታል ሆቴል በሃገራዊ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ በሰጠው መግለጫ ነው። 

በክልል ከተሞችና ከተማ አስተዳደሮች እየተጠራ ያለውንና ነገ ጥቅምት 28 ቀን 2014 ዓም በመስቀል አደባባይ የተጠራውን “የክተት ዘመቻ” እንደሚደግፍና ሚሊዮኖች የሰልፉ አካል ይሆናሉ የሚል ግምት እንዳለው አስታውቋል።

የተፎካካሪ ፓርቲዎች አባላትና ደጋፊዎች በሙሉ እየተደረገ ባለው ዘመቻ ከጦር ሀይሉ ጎን እንዲሰለፉ የጠየቀ ሲሆን፣ በመላው ሀገሪቱ የክተት አዋጅ እንዲደረግ ምክርቤቱ ጥያቄ እንዳቀረበም ተገልጿል። 

ምክር ቤቱ ዛሬ በሰጠው መግለጫ ላይ በትላንትናው እለት በአሜሪካ የተደረገውን የዘጠኝ ፓርቲዎች ጥምረትም አውግዟል። ጥምረቱ የስድስተኛውን ሀገራዊ ምርጫ ውጤትን ያጣጣለ ነው ሲልም ወቅሷል። 

ምክር ቤቱ በውግያ መሀል የሚደረጉ አሻጥሮች እንዳሉ ጠቁሞ፣ መንግስት ውስጡን እንዲፈትሽ ጠይቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ተመድንና ዓለም አቀፋዊ ሕግን ከእነ አሜሪካ አድራጊ ፈጣሪነት እናድን!

በገነት ዓለሙ በእኔ የተማሪነት፣ የመጀመርያ ደረጃ ተማሪነት ጊዜ፣ የመዝሙር ትምህርት...

የሰላም ዕጦትና የኢኮኖሚው መንገራገጭ አንድምታ

በንጉሥ ወዳጅነው ፍራንክ ቲስትልዌይት የተባሉ አሜሪካዊ ጸሐፊ ‹‹The Great Experiment...

ድህነት የሀብት ዕጦት ሳይሆን ያለውን በአግባቡ ለመጠቀም አለመቻል ነው

በአንድነት ኃይሉ ድህነት ላይ አልተግባባንም፡፡ ብንግባባ ኖሮ ትናንትም ምክንያት ዛሬም...