Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትፕሪሚየር ሊጉ በተያዘለት ፕሮግራም መሠረት ይቀጥላል ተባለ

ፕሪሚየር ሊጉ በተያዘለት ፕሮግራም መሠረት ይቀጥላል ተባለ

ቀን:

  • ዋሊያዎቹ ነገ በጆሃንስበርግ ጋናን ያስተናግዳሉ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ በነበረበት የማሟያ ጨዋታ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቀደም ሲል በተያዘለት ፕሮግራም መሠረት የሚቀጥል መሆኑ የሊጉ አክሲዮን ማኅበር አስታወቀ፡፡

ከኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ጋር ተያይዞ በአገር አቀፍ ደረጃ የተደነገገውን አስቸኳይ ጊዜ አዋጅን ተከትሎ ‹የሊጉ ቀጣይ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆናል?› በሚል ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖች ነበሩ፡፡

በጉዳዩ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የሊጉ አክሲዮን ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፉ፣ ይኼንን አስተያየት እስከሰጡበት ድረስ ጉዳዩን የተመለከተ፣ ከሚመለከተው አካል ምንም ዓይነት የደረሳቸው መመርያ የለም፡፡ በመሆኑም ፕሪሚየር ሊጉ ቀደም ሲል በወጣለት ፕሮግራም መሠረት በዚያው በሐዋሳ የሚቀጥል ስለመሆኑ ጭምር ተናግረዋል፡፡

ከጥቅምት 7 ቀን 2014 ዓ.ም. ጀምሮ በሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ሲካሄድ የሰነበተው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ፣ ብሔራዊ ቡድኑ ለነበረበት የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የመርሐ ግብር ማሟያ ጨዋታ ምክንያት ሊጉ እስከ ኅዳር 15 ቀን ድረስ እንደሚቋረጥ መነገሩ ይታወሳል፡፡

በሌላ በኩል ብሔራዊ ቡድኑ ባለፈው ማክሰኞ ጥቅምት 30 ቀን 2014 ዓ.ም. ወደ ደቡብ አፍሪካ ያመራ ሲሆን፣ በነገው ዕለት ከጋና አቻው ጋር ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ እንደሚጫወት ይጠበቃል፡፡ 

በሌላ በኩል ዋሊያዎቹ ኅዳር 2 ቀን ከጋና ጋር በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ላይ ከተጫወቱ በኋላ፣ በዚያው ወደ ዚምባቡዌ አቅንተው የመጨረሻውን የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታቸውን ኅዳር 5 ቀን የሚያደርጉ ይሆናል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...