Friday, December 1, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ ከአማካሪያቸው ጋር ሆነው የአፍሪካ ኅብረት ልዩ ወኪል የፖለቲካ ቀውሱን ለመፍታት እያደረጉ ያለውን ጥረት በተመለከተ እየተወያዩ ነው]

  • ሰውየው በእኛ ወገን ያለውን አቋም ከሰሙ በኋላ ወደ ሰሜን ሄደው ተመልሰዋል። 
    • ምን ይዘው ተመለሱ
    • በእነሱ በኩል የተያዘውን አቋም ለመረዳት ሞክረዋል። 
    • የእነሱ አቋም ምን እንደሆነ ማወቅ አልፈልግም፣ ግን ሰውየው የተረዱትን ማወቅ እፈልጋለሁ፣ ምን ተረዳሁ አሉ?
    • ያው ራስን በራስ የማስተዳደር መብታቸውን ለማስከበር የሚያደርጉት ትግል እንደሆነ እንደገለጹላቸው አሳውቀውናል። 
    • እና አመኗቸው
    • ሰውየው የእርሳቸው ሚና ሁሉንም ወገን ማናገርና ወደ መፍትሔ የሚያደርሰውን መንገድ መጠቆም እንደሆነ ነው የሚያምኑት። 
    • እሺ ከእነሱ ወገን ያለው አቋም ምንድነው አሉ? ማለቴ ፖለቲካዊ መፍትሔን በተመለከተ
    • በፖለቲካዊ መፍትሔ እንደሚስማሙ ነገር ግን ወደዚያ ለመሄድ ሦስት ቅድመ ሁኔታዎችን እንዳስቀመጡ ገልጸውላቸዋል። 
    • ቅድመ ሁኔታዎቹ ምንድናቸው
    • አንደኛ ከበባው ይቁም፣ ሁለተኛ ተጠያቂነት መስፈን አለበትና በሦስተኛ ደረጃና በመሠረታዊነት ደግሞ የሽግግር መንግሥት መቋቋም እንዳለበት ነው የነገሯቸው። 
    • የሽግግር መንግሥት መፍትሔ ከራሳቸው መምጣቱ ጥሩ ነው።
    • እንዴት ክቡር ሚኒስትር? ምን እያሉ ነው?
    • ምክንያቱም በሰሜን ያለውን የሥልጣን ክፍተት ለመፍታት ለእኛም አስቸጋሪ ነው የሚሆነው፣ ስለዚህ የሽግግር መንግሥት መፍትሔ ከራሳቸው መምጣቱ ጥሩ ነገር ነው ለማለት ፈልጌ ነው። 
    • ስተዋል፡፡
    • ምን?
    • ክቡር ሚኒስትር ስተዋል፣ እነሱ የሽግግር መንግሥት መቋቋም አለበት ያሉት እዚያ አይደለም። 
    • እና የት ነው?
    • እዚህ፣ ማዕከላዊ መንግሥቱ ፈርሶ የሽግግር መንግሥት ካልተቋቋመ ነው የሚሉት። 
    • እንደዚያ ነው?!
    • እንደዚያ ነው የሚሉት ክቡር ሚኒስትር።
    • ፍላጎታቸው ሌላ ነው አትለኝም እንዴ ታዲያ? ቆይ ቆይ በዚህ ብንስማማ የተቀረውን ምን ሊያደርጉ ነው?
    • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር?
    • ማዕከላዊ መንግሥት ተስማማና የሽግግር መንግሥት ይመሥረት አለ እንበል፣ የክልሎቹን ምን ሊያደርጓቸው ነው?
    • የክልሎቹ ሲሉ?
    • የክልል መንግሥታትን ማለቴ ነው?
    • እዚያም የሽግግር መንግሥት መቋቋም አለበት ነው የሚሉት።
    • እንዴት ሆኖ? ማነው የክልል መንግሥታትን ፍረሱና የሽግግር መንግሥት ይተካ የሚለው?
    • እውነት ብለዋል፣ ማን ነው የክልል መንግሥታት ላይ እንደዚያ የመወሰንልጣን ያለው? የፌዴራል መንግሥት እንደሆነ በክልሎች ላይልጣን የለውም፣ የፌዴራሉን መንግሥት ያቋቋሙት ክልሎች ራሳቸው ናቸው።
    • ለሰውየው ራስን በራስ ለማስተዳደር ነው የምንታገለው ብለዋል አላልከኝም እንዴ?
    • አዎ ብለዋል።
    • ታዲያ ሌሎች ክልሎችስ ተመሳሳይ መብት እንዳላቸው ዘንግተውት ነው
    • ዘንግተውት አይደለም። 
    • እና?
    • ያሉ መስሏቸው ነው፡፡
    • እነ ማን?
    • በክልል ሥልጣን ላይ ድሮ ያስቀመጧቸው።
    • እስካሁን

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሥራ አስፈጻሚው ስብሰባ በኋላ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በዕልልታ ተቀበሏቸው]

    • ምንድነው? ምን ተገኘ?!
    • ምን ተገኘ? ደስታ ነዋ፣ ደስታ፡፡
    • እኮ የምን ደስታ?
    • ሁሉም አመራር ወደ ጦር ግንባር ብላችሁ በመወሰናችሁ ነዋየቆየ ቢሆንም ትክክለኛ ውሳኔ ነው። 
    • ለአገርሽ እንዲህ ስትሆኚ አይቼ አላውቅም ነበር?
    • የእኔ ብቻ ስሜት አይመስለኝም፣ የሁሉም አገር ወዳድ ስሜት ነው፣ ቢዘገይም ዛሬም አልረፈደም፡፡ 
    • ከዛሬ ነገ ይታረማሉ ብለን፣ ለሁሉም ጊዜ አለው ብለን ያስታመምነው ውሳኔ ነው። 
    • እሰይእሰይየከተማው ወጣትም የት መሠለፍ እንዳለበት ከዚህ በኋላ መወሰኑ አይቀርም።
    • ምን ማለትሽ ነው? የት ነበር እስከ ዛሬ የሚሠለፈው?
    • ሲኒማ ቤት

[ክቡር ሚኒስትሩ ወደ ቢሯቸው እንደገቡ የእጅ ስልካቸው ጠራ፣ ሰሞኑን ደጋግመው የሚደውሉላቸው አንድ የአውሮፓ አገር ባለሥልጣን ነበሩ የደወሉት]

    • ጤና ይስጥልኝ ክቡር ሚኒስትር፡፡
    • ጤና ይስጥልኝ፣ እንደምን አለህ አምባሳደር?
    • ሰላም ነኝ፣ የአገር ውስጥ ሚዲያዎች የዘገቡትን ተመልክቼ ነበር የደወልኩት ክቡር ሚኒስትር፣ የተባለው እውነት ነው?
    • ምን ተባለ?
    • ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ አመራሮች እንዲዘምቱ መወሰኑን ነው ያነበብኩት። 
    • ልክ ነው፣ ውሳኔ ብቻ አይደለም እየተገበርነው እንገኛለን።
    • ክቡር ሚኒስትር ይህ ስህተት ነው፣ ወደ ተሳሳተ መንገድ እየሄዳችሁ ነው። 
    • እንዴት ብታስበው ነው አገርን የማዳን ዘመቻን ስህተት ነው ያልከው
    • ስህተት ነው ክቡር ሚኒስትርይህ አካሄዳችሁ ከእኛ ጋር ያላችሁን ግንኙነት የሚጎዳ ነው፡፡
    • እስካሁን ከጎዳችሁን በላይ?
    • እኛና እናንተ ለዓመታት የቆየ መልካም ወዳጅነት ነው ያለን።
    • እሱንማ አቆሸሻችሁት። 
    • ክቡር ሚኒስትር አሁን በወሰናችሁት መንገድ የምትቀጥሉ ከሆነ የምንሰጠውን ዕርዳታና ድጋፍ እንደምናቋርጥ አይጠራጠሩ፣ ይህ ደግሞ በችግር ውስጥ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ የሚጎዳ ነው። 
    • ኢትዮጵያዊን አታውቀውም ማለት ነው
    • አውቀዋለሁ እንጂ፣ እንዴት አላውቀውም?
    • ብታውቀውማ ያልከውን ለማለት አትደፍርም ብዬ ነው፣ ለማንኛውም እኔም አንድ ነገር ላረጋግጥልህ እፈልጋለሁ።
    • ምንድነው?
    • ያሻችሁን ብትወስኑ የሚደነቅ ኢትዮጵያዊ እንደማይኖር አረጋግጥልሃለሁ። 
    • ክቡር ሚኒስትር አይምሰልዎት፣ የሰው ልጅ በችግር ውስጥ ሲሆን ምን እንደሚያደርግ አይታወቅም።
    • አትጨነቅ። 
    • ለምን አልጨነቀም
    • ምክንያቱም ኢትዮጵያዊነት በልቶ ከማደር በላይ ከፍ ያለ ነው!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...