Friday, December 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊከ400 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሦስት ራዳሮች ሊተከሉ ነው ተባለ

ከ400 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሦስት ራዳሮች ሊተከሉ ነው ተባለ

ቀን:

ቅፅበታዊ የአየር ሁኔታን ለመተንበይ ያስችላሉ ተብሏል

ለአየር ሁኔታ መከታተያ የሚሆኑ ሦስት ራዳሮችን 400 ሚሊዮን በላይ በሆነ ወጪ ሊተክል መሆኑን ብሔራዊ ሚቲዮሮሎጂ ኤጀንሲ አስታወቀ።

ኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ክንፈ ይለ ያም ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ የኢትዮጵያ መንግት ከፊንላንድ መንግት ባገኘው የገንዘብ ድጋፍና ብድር የሚተከሉት እነዚህ ራዳሮች በሁለት መት ተኩል ጊዜ ውስጥ ተጠናቀው ይጀምራሉ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እስካሁን አገልግሎት እየሰጠ የሚገኘው ራዳር አንድ ብቻ እንደሆነና ከሦስት መታት በላይ በሥራ ላይ የሚገኝ መሆኑን፣ የአየር ሁኔታን ለመቆጣጠርና ከዚህ በፊት ለተሞከሩት የደመና ማበልራዎች ማገልገሉን አስረድተዋል፡፡

ራዳበአማራ ክልል ሰሜን ጎንደር ዞን ሻውራ በተባለ ቦታ የሚገኝ እንደሆነና በ80 ሚሊን ብር ወጪ መገንባቱን የገለጹት ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ፣ 150 ኪሎ ሜትር ዙሪያ ክብ ውስጥ መረጃዎችን በውጤታማነት ማስተላለፍ የሚችል ቴክኖሎጂ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አሁን የሚተከሉት ራዳሮች እስከ 450 ኪሎ ሜትር ምል የማንሳት አቅም እንዳላቸው እስከ 250 ኪሎ ሜትር በጥራትና በበቂ ሁኔታ መረጃ ማስተላለፍ እንደሚችሉ አክለዋል፡፡

የአየር ሁኔታ መከታተያ ራዳሮቹ በስት ቦታዎች የሚተከሉ ሲሆን በመካከለኛው ኢትዮጵያ ክፍል በሰሜን ሸዋ ዞን እነዋሪ በተባለ ቦታ፣ በምራብ ኢትዮጵያ መቆ በተባለ ቦታ እንዲሁም በደቡብ ኢትዮጵያ ሃላባ ውስጥ እንደሆነ አቶ ክንፈ ገልጸዋል፡፡ በሰሜን ሸዋ ዞን እነዋሪ የሚተከለው የመጀመሪያው ራዳር መጪው ክረምት ከመግባቱ በፊት ይጠናቀቃል ተብሎ እንደሚጠበቅም ገልጸዋል፡፡

‹‹የራዳሮቹ ዋጋ እንደ አካባቢው ይለያያል፣ እያንዳንዳቸው ከ2.5 እስከ ሦስት ሚሊን ዶላር የሚያስወጡ ናቸው፤›› ሲሉ አቶ ክንፈ አስረድተዋል፡፡ 

ራዳሮቹን ለመትከል የሚያስፈልጉ መሪያዎች ፊንላንድ በሚገኙ ድርጅቶች በመመረት ላይ መሆናቸውን ገልጸው ግብዓቶቹ ተመርተው እንዳለቁ በሚቀጥሉት ጥቂት ወራት ወደ ገር ውስጥ በማስመጣት ወደ ተከላ እንደሚገባ  አስረድተዋል፡፡

እንደ አቶ ክንፈ ገለጻ፣ አሁን ሽፋን ያስፈልጋቸዋል ተብለው የተለዩት አካባቢዎች በብዛት ዝናብ የሚገኝባቸውና ጎርፍ የሚከሰትባቸው ቦታዎችን ታሳቢ ያደረጉ ሲሆን ራዳሮቹ በነዚህ አካባቢዎች የሚኖርን የአየር ሁኔታ በመከታተልና በመቆጣጠር የረም ጊዜ መረጃ ለመመዝገብ የሚያስችሉ ናቸው፡፡ እነዚህን መረጃዎች መረት በማድረግ ለግብርና፣ ለጤና፣ ለግንባታ ዘርፍ፣ ለግድቦችና ለሌሎችም ለከባቢ አየር ተጋላጭ የሆኑ ዘርፎች የዝናብ፣ የጎርፍ፣ የድርቅና የንፋስበተሻለ ጥራት ለመተንበይና ለመመዝገብ ከፍተኛ ሚና ይኖራቸዋል ብለዋል፡፡

ከዚህ በፊት የአየር ትንበያ የሚራው ከተለያዩ አገሮች ሳተላይቶች ከሚሰበሰቡ መረጃዎች መሆኑንና እያንዳንዱ ቦታ የአየር ሁኔታ መረጃ ለማግኘት አስቸጋሪ እንደሆነ  የጠቀሱትበብሔራዊ ሮሎጂ ኤጀንሲ ተባባሪ ተመራማሪ አቶ ለታ በቀለ ሲሆኑ፣ የሚተከሉት ራዳሮች የተለዩ ቦታዎችን የአየር ሁኔታ በተሻለ ጥራት ለመተንበይ እንደሚያስችሉ ይናገራሉ፡፡ ‹‹እስካሁን የአጭር ጊዜ ትንበያ የሚባለው ቢያንስ የአንድ ቀን ነው፡፡ እነዚህ ራዳሮች ግን ከአምስት ደቂቃ ጀምሮ ያሉ ቅበታዊ የአየር ሁኔታ ትንበያ ለመራት የሚያችል ቴክኖሎጂ ያላቸው ናቸው፤›› በማለት አስረድተዋል፡፡

በአጠቃላይ በገሪቱ የሚገኝ የአየር ሁኔታን በበቂ መጠን ለመከታተል 12 ራዳሮች እንደሚያስፈልጉ በጥናት መታወቁን የጠቆሙት የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ ክንፈ  አሁን ያለውን ጨምሮ በሁለት መት ተኩል የሚተከሉት ሦስት ራዳሮች ሲጠናቀቁ የተሻለ የአየር ሁኔታ ቁጥጥርና ክትትል አቅምን እንደሚፈጥሩ አስረድተዋል፡፡

ሌሎች ስምንት ራዳሮችን ለመትከል የሚያስፈልገው ፕሮጀክት ፕሮፖዛል መዘጋጀቱን  የጠቆሙት አቶ ክንፈ ‹‹ቴክኖሎጂው አዲስ ስለሆነ በአንድ ጊዜ ሁሉም ቢተከሉ ውጤታማ ላይሆ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ባሉት እየተማርን ሌሎቹን ቀስ በቀስ እናስፋፋለን፤›› ብለዋል፡፡

በምሥጋ ፈንታው

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...