Friday, June 2, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ከ49 ቢሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ዝውውር ያሳለጠው ፕሪሚየም ስዊች ሶሉውሽን

- ማስታወቂያ -

ተዛማጅ ፅሁፎች

ከተመሠረተ አሥረኛ ዓመቱን የያዘውና በዋናነት በአምስት ባንኮች የተመሠረተው ፕሪሚየር ስዊች ሶሉውሽን (ፒኤስኤስ) ባለፉት ዘጠኝ መታት ከ49 ቢሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ማንቀሳቀስ ሒደቶችን ማካሄድ መቻሉን ገለጸ፡፡

ኩባንያው የተመሠረተበትን አሥረኛ ዓመት የምሥረታ በዓልና የ2013 የሒሳብ ዓመት አፈጻጸሙን በማስመልከት በሰጠው መግለጫ በዘጠኝ ዓመታት ውስጥ 49 ቢሊዮን ብር በኤቲኤም ማሽን በኩል ማንቀሳቀስ ችሏል፡፡   

ፒኤስኤስ በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት በአጠቃላይ የገንዘብ መጠናቸው 13.9 ቢሊዮን ብር በላይ የሆኑ 15.1 ሚሊዮን የገንዘብ ማንቀሳቀስ ሒደቶችን ያስተናገደ መሆኑን፣ የኩባንያው የዳይሬክተሮች ቦርድ ሊቀመንበር አቶ ፀሐይ ሽፈራው ገልጸዋል፡፡ ይህ ፒኤስኤስ ሥራ ከጀመረበት ዓመት ጀምሮ ባለፉት ዘጠኝ ዓመታት ውስጥ በጥቅሉ ከ49 ቢሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ብዛታቸው ከ56 ሚሊዮን በላይ የገንዘብ ማውጣት ሒደቶችን በኤቲኤም አማካይነት ማስተናገድ ችሏል፡፡

የፒኤስኤስ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዮሴፍ ክብረት በበኩላቸው፣ ከባንያው አንድ ሚሊዮን የሚጠጋ የፒኤስኤስአር የያዙ ካርዶች በማተምና ለአባል ባንኮች በማድረስ የባንኮቹን ፍላጎት ያማከለ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡ ይህ ቁጥር ፒኤስኤስ ከተመረተበት መት ጀምሮ ለገበያ ያሠጫቸውን የክፍያ ካርዶች ብዛት 3.1 ሚሊዮን ብር በላይ ማድረስ መቻሉንም አመልክተዋል፡፡ 

ሞባይል ቀፎ አማካይነት በሚሰጥ ትዕዛዝ ከኤቲኤም ገንዘብ የማውት የካርድ አልባ አገልግሎት ጭማሪ ያሳየ ሲሆን፣ በተያዘው በሒሳብ ዓመት ከ7.8 ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ያላቸው ብዛታቸው 8,244 የሆኑ የገንዘብ ማው ደቶችን ያሳለጠ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ በሌላ በኩል በተጠናቀቀው የሒሳብ ዓመት የክፍያ መቀበያ ማሽኖችን በመጠቀም በአባል ባንኮችና በዓለም አቀፍ የክፍያ ካርዶች አማካይነት 147,321 የገንዘብ ማንቀሳቀስ ሒደቶችን ወይም ግምቱ 428 ሚሊዮን ብር በላይ የግዥ፣ ንዲሁም የገዘብ ማውጣት ደቶችን ማከናወን ችሏል፡፡ ድርጅቱ ራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ የተፈሙ የፖዝ ትራንዛክሽኖች ቁጥር አበረታች ማሪ እያሳየ ቢመጣም፣ በአንፃሩ በኢትዮጵያ ውስጥ የክፍያ መቀበያ ማሽኖችን በመጠቀም የሚደረጉ ግብይቶች አሁንም በዝቅተኛ ደረጃ የሚገኙ መሆናቸውንም ጠቅሰዋል፡፡ ፒኤስኤስ የክፍያ መረቡን ከማስፋት አኳያ በሒሳብ ዓመቱ 67 ተጨማሪ ኤቲኤም ማሽኖች፣ እንዲሁም 771 የክፍያ መቀበያ ማሽኖች ከፒኤስኤስ ሥርዓት ጋር ተገናኝተው አገልግሎት መስጠት በመጀመራቸው፣ በአጠቃላይ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የኤቲኤም ማሽኖች ቁጥር 1,070፣ እንዲሁም የክፍያ መቀበያ ማሽኖች ቁጥር 2,565 አድርሶታል፡፡

ፒኤስኤስ ከተቋቋመበት ዓላማ አንፃር መመዘን ያለበት ከአገልግሎት ጥራትና ስፋት አንፃር ቢሆንም፣ በዚህ በጀት ዓመት ከመቼውም ጊዜ በተሻለ ያልተጣራ ትርፍ ሦስት ሚሊዮን ብር በላይ ያገኘ መሆኑን ኩባንያው አመልክቷል፡፡ ይህ የትርፍ መጠንም ካለፈው መት ጋር ሲነጻጸር 61.62 በመቶ ጭማሪ እንዳሳየም ገልጿል፡፡

ይህ በእንዲህ ንዳለ ፒኤስኤስ በ2013 ሒሳብ ዓመት አቅዶ የነበረውን የትራንስፎርሜሽን ፕላን ቀረፃ ተግባራዊ በማድረግ ፒደብሊውሲ (PWC) የተባለ ለም አቀፍ አማካሪ በመቅጠር የድርጅቱን አምስት መት ስትራቴጂ ወይም የትራንስፎርሜሽን ቅድ በጥምር ሠርቶ ያጠናቀቀ ሲሆንይህ ስትራቴጂ ቅድ ፒኤስኤስ ተስፋ ሰጪ የሆኑ ሥራዎችን በላቀ አፈጻጸ ተግባራዊ ያደርግ ያግዘዋል ተብሏል፡፡

የፒኤስ ኤስ ዋነኛ ተጣማሪ ባንኮች አዋሽ፣ ንብ፣ ኅብረት፣ ብርሃን፣ አዲስ ኢንተርናሽናልና የኦሮሚያ ኅብረት ሥራ ባንኮች ናቸው፡፡

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች