Saturday, December 2, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ክቡር ሚኒስትሩ የተስፋፋው የሰሜን ጦርነት ያደረሰውን ጉዳት ጎብኝተው ከተመለሱ በኋላ አማካሪዎቻቸውን ሰብስበው እየተወያዩ ነው]

  • በሰሜኑ አካባቢ የተስፋፋው ጦርነት ያደረሰው ጉዳት የጎበኛችሁትን ይመስላል፣ ለትውልድ የሚሻገር ጉዳትን ለማድረስ ከማቀድና ከመፈጸም የሚበልጥ ክፋት ምን ሊኖር ይችላል
  • ክቡር ሚኒስትር እኔ ወገን በወገኑ ላይ በዚህ ደረጃ ይጨክናል ብዬ አስቤ አላውቅም፣ ዓላማው ግን ነው።
  • ምንድነው ዓላማው?
  • በጦርነቱ ብንሸነፍ እንኳን መንግሥት ተረጋግቶ እንዳይቀጥል የዓመታት የቤት ሥራ እንስጠው ብለው ዕቅድ አውጥተው የተገበሩት ሰይጣናዊ ሥራ ነው፣ ጦርነቱን ብንሸነፍም በቀጣይዝቡ በኢኮኖሚ ችግርና በሕክምናጦት ተማርሮ መንግሥት ላይ እንዲነሳ እናደርገዋለን ብለው አቅደው የፈጸሙት ክፋት ነው የሚመስለኝ።
  • ክቡር ሚኒስትር እኔም በዚህ ሐሳብ እስማማለሁ፣ እንዴት የሰው ልጅ ሆን ብሎ የጤና ተቋማትን እየለየ ያወድማል? ማንን ለመጉዳት ነው? ከአምስት ሺሕ በላይ የጤና ተቋማትን እኮ ነው ያወደሙት?
  • ክቡር ሚኒስትር ልክ ነው፣ በዕቅድ የተፈጸመ መሆኑን እንዳምን ያደረገኝ ደግሞ አንድም የወደመ የጤና ተቋም SSA ላይ ተመዝግቦ አለማየቴ ነው።
  • ምንድነው SSA ያልከው?
  • Surveillance system for attacks on health care (SSA) ይባላል፣ የዓለም ጤና ድርጅት በየአገሩ በጤና ተቋማት ላይ የሚደርሱ ጥቃቶች እንዲመዘገቡ ብሎ በሥራ ላይ ያዋለው መተግበሪያ ነው። 
  • እህ…
  • ይህ መተግበሪያ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጭምር ዕውቅና የተሰጠውና ጥቃት ያደረሱ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ የሚረዳ ነው፣ በየአገሩ በጤና ተቋማትና ባለሙያዎች ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶችን ያሳያል፣ የየአገሩን ስም መተግበሪያው ላይ በማስገባት የደረሱ ጉዳቶችን መረጃ ማግኘት ይቻላል።
  • በኢትዮጵያ የደረሰው ጉዳትም ተመዝግቧል?
  • የሚገርመው እኮ እሱ ነው ክቡር ሚኒስትር፣ የኢትዮጵያን ስም ሲያስገቡ ዜሮ ነው የሚመጣው፣ መረጃው ምንም ጉዳት ወይም ጥቃት የለም ነው የሚለው። 
  • እንዴት ሊሆን ይችላል? ዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ተቋማት ጭምር የሚያውቁት መረጃ አይደለም እንዴ?
  • ክቡር ሚኒስትር ነገሩን መመርመር ያለብን ይመስለኛል፣ ሆን ተብሎ ለማድበስበስ የተሴረ ይመስላል፣ ምክንያቱም
  • ምክንያቱም ድርጅቱ የሚመራው በእነሱ ወገን ነው። 
  • እነሱ ማለት
  • የጤና ተቋማቱን ባወደሙት፡፡ 
  • አሃ… አሃ… የጤና ድርጅቱን የሚመራው ሰው?
  • ትክክል። 
  • ጥሩ መረጃ ነው!

[ክቡር ሚኒስትሩ ሥራ አመሻሽተው ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ባለቤታቸው የቴሌቪዥኑን ቻናል እየቀያየሩ ሲመለከቱ አገኟቸው]

  • ምንድነው የምትፈልጊው? አንዱ ቻናል ላይ አትረጊም እንዴ? 
  • እንዴት ብዬ ልረጋጋ? እነሱ እየተቅበዘበዙ አይደለም እንዴ?
  • እነማንን ነው የምትይው?
  • ማፈግፈግ አይደለም፣ ሥልታዊ የቦታ ለውጥ ነው ያሉትን ማለቴ ነዋ፡፡
  • አይ አንቺ…
  • እንዲያውም ቴሌቪዥኑ ይቅርብኝና አንተ ንገረኝ እስኪ?
  • ምን ልንገርሽ?
  • የት እንደ ደረሱ
  • ጋሸናንና ላሊበላን ለመያዝ እየተዋጉ ነው።
  • ጋሸናና ላሊበላ?
  • አዎ።
  • እንደገና?
  • እንደገና ማለት?
  • የቦታ ለውጥ አደረግን ያሉት ከላሊበላናጋሸና አልነበረም እንዴ?
  • አዎ፣ ከጋሸናና ከካሳጊታ ሲለቁ ነበር እንደዚያ ያሉት፣ ጎበዝ ነሽ አትዘነጊም?
  • እና ላሊበላን ድጋሚ ለመያዝ እየተዋጉ ነው? ከምርህ ነው?
  • ስነግርሽ? አዎ።
  • ውይተምታቶባቸው እንዳይሆን?
  • ምኑ?
  • ላሊበላ ላይ ያተኮሩበት ምክንያት፡፡
  • እንዴት?
  • በቃ ተምታቶባቸው ነው የሚሆነው… አይ…
  • ምኑ ተምታቶባቸው?
  • ቤተ ጊዮርጊስ ተምታቶባቸው ሳይሆን አይቀርም፡፡
  • ላሊበላ ቤተ ጊዮርጊስ?
  • አዎ…
  • ከምን ሊምታታባቸው ይችላል?
  • ከቤተ መንግሥት?
  • ምን…?
  • ያገኛችሁትን ቤተ መንግሥት ያዙ ተብለው ነውደጋግመው ወደ እዚያ የሚሄዱት፡፡
  • ወዴት?
  • ወደ ቤተ ጊዮርጊስ!
  • አይ አንቺ…!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

የመቃወም ነፃነት ውዝግብ በኢትዮጵያ

ስሟ እንዳይገለጽ የጠየቀችው በአዲስ አበባ ከተማ በተለምዶ የሾላ አካባቢ...

የሲሚንቶን እጥረትና ችግር ታሪክ ለማድረግ የተጀመረው አጓጊ ጥረት

በኢትዮጵያ በገበያ ውስጥ ለዓመታት ከፍተኛ ተግዳሮት በመሆን ከሚጠቀሱ ምርቶች...

የብሔር ፖለቲካው ጡዘት የእርስ በርስ ግጭት እንዳያባብስ ጥንቃቄ ይደረግ

በያሲን ባህሩ በሪፖርተር የኅዳር 9 ቀን 2016 ዓ.ም. ዕትም “እኔ...

ሀብቱንና ትርፉን እያሳደገ የቀጠለው አዋሽ ባንክ

አዋሽ ባንክ በአዲስ አበባ ከተማ አዲስ ዋና መሥሪያ ቤት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ የሩብ ዓመት የሥራ አፈጻጸማቸውን ለተከበረው ምክር ቤት ካቀረቡ በኋላ ከምክር ቤቱ አባላት የሚነሱ ጥያቄዎችን እየተቀበሉ ማብራሪያ በመስጠት ላይ ናቸው]

ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ለሕዝብ ይፋ ያደረገው ነገር ከምን እንደደረሰ ቢያብራሩልን? ምንድነው ይፋ ያደረገው? ጥያቄውን ትንሽ ቢያብራሩት? ከአራት ዓመት በፊት በኦጋዴን አካባቢ ነዳጅ መገኘቱን ለሕዝብ በቴሌቪዥን አብስሮ...

[ክቡር ሚኒስትሩ አንድ የካቢኔና የማክሮ ኢኮኖሚ ኮሚቴ አባል የሆኑ ከፍተኛ አመራር የሚያቀርቡትን ቅሬታ እያደመጡ ነው] 

ክቡር ሚኒስትር እየሆነ ያለው ነገር በእጅጉ ስላሳሰበኝ ነው በአካል አግኝቼ ላነጋግርዎት የፈለግኩት። ጥሩ አደረግህ፣ ምን አሳሳቢ ነገር ገጥሞህ ነው? ክቡር ሚኒስትር ተወያይተንና ተግባብተን ያስቀመጥናቸው አቅጣጫዎች፣ በተለይም...

[ጉባዔው በወቅታዊ አገራዊ ጉዳዮች ላይ ክቡር ሚኒስትሩን ለመጠየቅና ምላሽና ማብራሪያቸውን ለማድመጥ ተሰብስቧል። የጉባዔው አባላትም ማብራሪያ የሚሹ ጥያቄዎቻቸውን ለክቡር ሚኒስትሩ እያቀረቡ ነው]

ክቡር ሚኒስትር፣ ይህ ጉባዔ ለሚያነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት በመካከላችን ስለተገኙ አመሰግናለሁ። ክቡር ሚኒስትር፣ ኢትዮጵያ ባለፈው ዓመት የብሪክስ አባል እንድትሆን የሰጡት በሳል አመራር የሚደነቅ ነው። አገራችን...