Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜና‹‹ከ85 ዓመታት በኋላ እዚህ ጄኔቫ ላይ ታሪክ ራሱን ደግሟል›› አቶ ዘነበ...

‹‹ከ85 ዓመታት በኋላ እዚህ ጄኔቫ ላይ ታሪክ ራሱን ደግሟል›› አቶ ዘነበ ከበደ- በስዊዘርላንድ የኢትዮጵያ አምባሳደር

ቀን:

በአውሮፓ ኅብረት የቀረበው የውሳኔሳብ በአብላጫ ድምፅ ጸድቋል

የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ጄኔቫ በሚገኘው የተመድ ጽሕፈት ቤት ባለፈው ዓርብ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ባካሄደው አስቸኳይ ልዩ ስብሰባ ላይ፣ የመንግሥታቸውን አቋም የተመለከተ ንግግር ያደረጉት በስዊዘርላንድ የኢትዮ አምባሳደር አቶ ዘነበ ከበደ፣ ታሪክ ራሱን ደግሞ ኢትዮጵያ 85 ዓመታት በኋላ ሉዓላዊነቷን ለማስከበር በተመድ የጄኔቫ ጽሕፈት ቤት መቆሟንና አሁንም ለባለብዙ ወገን የዓለም አስተዳደር ያላት እምነት፣ ሉዓላዊነቷን ለማስጠበቅ እንዳልረዳት ገለጹ።

ኢትዮጵያ የዓለምዝቦች የጋራ ደኅንነት እንዲከበርና የጋራ ትብብርና የባለብዙ ወገን ሥርዓት የሰፈነበት ዓለም አቀፋዊ አስተዳደር እንዲሰፍን ባላት ፅኑ እምነት፣ የተባባሩት መንግሥታት መሥራች አገር እንደሆነች የገለጹት አምባሳደሩ፣ 85 ዓመታት በፊት በፋሽስታዊው የጣሊያን መንግሥት የተፈጸመባትን ወረራ፣ በጄኔቫ የዓለም መንግሥታት መድረክ ተገኝታ የደረሰባትን በደል በማቅረብ፣ ሉዓላዊነቷን ለማስከበር ያደረገችው ጥረት ሰሚ ጆሮ ማጣቱን አስታውሰዋል።

85 ዓመታት በኋላ ዓርብ ታኅሳስ 8 ቀን 2014 ዓ.ም. በጄኔቭ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የተገኘችው በተመሳሳይ ሁኔታ ሉዓላዊነቷን ለማስከበር እንደሆነ አምባሳደሩ ገልጸዋል።

በዴሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ መንግሥቷን ለመከላከል፣ ሰላምንና የወደፊት ሕዝቦቿን ዕጣ ፈንታ የማረጋገጥ መብቷን ለማስከበር በመሞከሯ፣ በሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ ላይ ቀርባ የፖለቲካ ጥቃት እንዲደርስባት መደረጓን ተናግረዋል።

‹‹85 ዓመታት በኋላ እዚህ ጄኔቫ ላይ ታሪክ ራሱን ደግሟል፡፡ ለባለብዙ ወገን ሥርዓት ለመፍጠር ያለን ቁርጠኝነት አገራችንን ለመጠበቅ አልረዳንም›› ያሉት አምባሰደሩ፣ ‹‹85 ዓመታት በኋላም መልቲላተራሊዝም እንደገና በኒዮኮሎኒያሊስት አስተሳሰብ እየተጠለፈ ነው፤›› ብለዋል።

ኢትዮጵያ ከውስጧ የተነሳ አዋኪ የገጠማት ቢሆንምዘመናዊ ቅኝ ግዛት ለመፈጸም የሚተጉ ኃይሎች በኢትዮጵያ ላይ የፖለቲካ ፍላጎታቸውን ለመጫን ይህንን የውስጥ አዋኪ ኃይል በመደገፍ እያጎለበቱት እንደሚገኙና በዚህም የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት እየፈተኑ እንደሚገኙ ተናግረዋል።

በዘመናዊ ቅኝ ገዥዎች ምክንያት የበርካታ አገሮችን መፍረስንና አለመረጋጋት ከቅርብ ዓመታት ወዲህ እያየን በመሆኑ በቃ ሊባል ይገባል ያሉት አምባሳደር ዘነበ፣ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ተልዕኮናራ፣ የእነዚህ ኃይሎችን ድብቅ የፖለቲካላማዎች ማራመድ እንዳልሆነም በአጽንኦት ተናግረዋል።

‹‹ባለፈው የቅኝ ግዛት ወረራ ለመከላከል ብቻችንን ቆመን ነበር። ዛሬ ግን ብቻችንን አይደለንም። ኢትዮጵያ የገጠማትን ዓይን ያወጣ የፖለቲካ ጫና ከሌሎች አገሮች ጋር ተባብራ የባለብዙ ወገን የዓለም አስተዳደር እንዲሰፍን ትታገላለች፤›› ብለዋል።

በአውሮፓ ኅብረት የቀረበውን የውሳኔሳብ ለማጽደቅ በተሰጠው ድምፅ፣ የውሳኔ ሐሳቡ 21 አገሮች ድጋፍ 15 አገሮች ተቃውሞና 11 አገሮች ድምፀ ተዓቅቦ በአብላጫ ድምፀ ጸድቋል።

ውይይቱ በተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት በተካሄደበት ወቅት፣ ካሜሮን የአፍሪካ ቡድንን በመወከል የቀረበውን የውሳኔሳብ አፍሪካዊያን እንደሚቃወሙ ቢገለጽም፣ የተሰጠው ድምፅ ይፋ ሲደረግ ግን ከአፍሪካ አገሮች መካከል ሱዳን፣ ሴኔጋል፣ ሊቢያ፣ ማላዊና ቶጎ ድምፀ ተዓቅቦ ማድረጋቸው ታውቋል።

የፈቀደው የውሳኔ ሐሳብ ከዚህ ቀደም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን፣ ከተመድ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ጋር በጥምረት ያደረጉት ምርመራ ውጤትን መነሻ በማድረግ፣ ተጨማሪ ምርመራ የሚያደርግ ዓለም አቀፍ የባለሙያዎች ቡድን እንዲሰማራ የሚወስን ነው።

ዓለም አቀፍ መርማሪ ቡድኑ የአንድ ዓመት ቆይታ እንዲኖረውና የሚላከው ቡድን ከሚያደርገው ምርመራ በተጨማሪ፣ የሽግግር ፍትሕ ተግባራዊ የሚደረግበትን፣ እርቅና ተጠያቂነት የሚሰፍንበትን እንዲሁም፣ ሰብዓዊ ጥሰት የደረሰባቸው ማገገም እንዲችሉ ምክረ ሐሳብና የቴክኒክ ድጋፍ የመስጠት ኃላፊነት እንደሚኖረውም ይገልጻል።

የውሳኔሳቡ ቢፀድቅም የኢትዮጵያ አምባሳደር ውይይቱ ሲጀመር አንስቶ የውሳኔሳቡ ቢፀድቅ እንኳን፣ በኢትዮጵያ መንግሥት ተቀባይነት እንደማይኖረው ገልጸዋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...