Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትእግር ኳስ ፌዴሬሽን በኮሎኔል አወል አብዱራሂም ምትክ አቶ አበበ ገላጋይን ሾመ

እግር ኳስ ፌዴሬሽን በኮሎኔል አወል አብዱራሂም ምትክ አቶ አበበ ገላጋይን ሾመ

ቀን:

በአርባምንጭ ከተማ ዛሬ ታህሣሥ 23 ቀን 2014 ዓም 13ኛ ጠቅላላ ጉባዔውን  ያካሄደው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን፣ ተጓድሎ የነበረውን የምክትል ፕርዜዳንት  ምትክና  የሴቶች ጉዳይ ኮሚቴ ሰብሳቢ ሸሙት አፀደቀ።
የፌዴሬሽኑ ሥራ  አስፈፃሚ ኮሚቴ  ሲያከናውናቸው በነበረው ሰብሰባ ላይ ለአንድ አመት ሳይገኙ የቆዩትን የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕረዚዳንት ኮሎኔል አወል አብዱራሂም ምትክ፣  የፌዴሬሽኑ የስራ አስፈፃሚ አባል የሆኑትን አቶ አበበ ገላጋይን ሾመ። 
በኢትዮጵያ ኦሊምፒክ ኮሜቴ መደበኛ ጉባዔ ላይ ያለ ፌዴሬሽኑ እውቅና ተሳትፈዋል ተብለው በጊዜያዊነት ታግደው የነበሩትን ወይዘሮ ሶፍያ አልማሙን ዕገዳ አንስቷል። 
የቅድሞ ደደቢት እግር ኳስ ክለብ መስራችና የፌዴሬሽኑ ምክትል ፕረዚዳንት ኮሎኔል አወል 
በ1983 ዓ.ም  ህወሓት አገሪቷን መቆጣጠሩን ተከትሎ፣ የአገር መከላከያ ስራዊት የሎጄስቲክና የንብረት ክፍል ኃላፊ በመሆን አገልግለዋል።  ደደቢት የወንዶች እግር ኳስ ክለብን አቋቁመው ለ16 ዓመታት መምራት የቻሉት ኮሎኔል አወል፣ በ2005 ዓ.ም  የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን ለመጀመሪያ ጊዜ ከክለቡ ጋር ማንሳት ችለዋል።  
ከታህሳስ 23 እሰከ 24 ቀን 2013 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባሄውን በአርባ ምንጭ ያካሄደው ፌዴሬሽኑ፣ የቀጣዩን ጠቅላላ  ጉባዔ በጎንደር ከተማ እንደሚያደርግ አስታውቋል። 

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...