Thursday, June 1, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊበኮምቦልቻ ደረቅ ወደብ ለወደሙ ኮንቴይነሮች ካሳ አይከፈልም ተባለ

በኮምቦልቻ ደረቅ ወደብ ለወደሙ ኮንቴይነሮች ካሳ አይከፈልም ተባለ

ቀን:

የኢትዮጵያ ባህርና ሎጂስቲክስ አገልግሎት ድርጅት በሰሜን ኢትዮጵያ በነበረው ጦርነት ወቅት በኮንቴይነሮች ላይ የደረሰው ጉዳት ከቁጥጥሩ ውጪ (Force Majeure) በመሆኑ፣ ተጠያቂ ሊሆን እንደማይችልና ካሳ እንደማይከፍል አስታወቀ።

የድርጅቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሮባ መገርሳ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣በኮምቦልቻ ደረቅ ወደብ ዕቃ ይዘው የነበሩ 252 ኮንቴይነሮች በአሸባሪነት በተፈረጀው ሕወሓት ታጣቂ ቡድን ወድመዋል፣ ተዘርፈዋል።

ኮንቴይነሮቹ ከውጭ የገቡ ማሽኖችን፣ የኢንዱስትሪ ግብዓቶችን፣ ምግብና መድኃኒቶችና ሌሎች የደንበኞች ዕቃዎችን የያዙ ነበሩ።

‹‹ኮንቴነሮቹ የተለያዩ ዕቃዎችን ይዘው ነበር። በተጨማሪም ራሳችን ቢሮዎችና ንብረቶች ወድመዋል። ችግሮቹ ከቁጥጥራችን ውጭ የተፈጠሩ ስለሆኑ ካሳ መክፈል አንችልም።  ነገር ግን ጉዳቶቹን ከጉምሩክ ኮሚሽን ጋር ሆነን በጋራ ጠናን ነው፤›› ብለዋል።

ኮምቦልቻ ደረቅ ወደብ ከሞጆና ከቃሊቲ ቀጥሎ ትልቁ ደረቅ ወደብ ሲሆን፣ ለሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ዋነኛው የወጪ ንግድ ማዕከል ነበረ። ድርጅቱ በመቀሌም  ደረቅ ወደብ ያለው ሲሆን፣ በጦርነቱ ምክንያት ማንቀሳቀስም ሆነ ስላለበት ሁኔታ መናገር ባይቻልም፣ ከኮምቦልቻ የተለየ ዕጣ ፈንታ ይኖረዋል ተስፋ እንደሌለ ጠቁሟል፡፡

የኮምቦልቻ ደረቅ ወደብ በዓመት እስከ ሃምሳ ሚሊዮን ብር ገቢ ያስገኝ የነበረ ቢሆንም፣ በዚህ ዓመት ግን ገቢው ሊያሽቆለቁል እንደሚችል አቶ ሮባ ጨምረው ገልጸዋል።

ለአንድ ዓመት በነበረው ጦርነት በንብረትና በኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች ላይ ዘርፈ ብዙ ጉዳት የደረሰ ሲሆን፣ መንግሥት ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው መመለስ እንዴት እንደሚቻል ጥናት እያደረገ መሆኑን አስታውቋል።

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በአዲስ አበባ በድምቀት ተከበረ

የአዛርባጃን ኤምባሲ  የአዛርባጃንን ብሄራዊ ቀን በትላንትናው ዕለት አከበረ። ሰኞ...

የመንግሥትና የሃይማኖት ልዩነት መርህ በኢትዮጵያ

እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሃይማኖት ተቋማት አዎንታዊ ሚና የጎላ...

ሐበሻ ቢራ ባለፈው በጀት ዓመት 310 ሚሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ

የአንድ አክሲዮን ሽያጭ ዋጋ 2,900 ብር እንዲሆን ተወስኗል የሐበሻ ቢራ...