Friday, December 8, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊየአርሶ አደሮችን ድካም እያቃለለ ያለው የአጨዳ ፕሮግራም

የአርሶ አደሮችን ድካም እያቃለለ ያለው የአጨዳ ፕሮግራም

ቀን:

ከአዲስ አበባ ከተማ በ164 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘውና የሰሜን ሸዋ ዞን ሞረትና ጅሩ ወረዳ መቀመጫ ከሆነችው እነዋሪ ከተማ አቅራቢያ ያለ ሰፊ እርሻ ላይ፣ ጤፍና ስንዴ የሚያመርቱት አርሶ አደር አቶ እንደራስ ቸርነት በመስከረም ወር ከዘመቱበት የሰሜን ኢትዮጵያ ጦርነት ከተመለሱ ጥቂት ጊዜያቸው ነው፡፡ በክረምቱ ወራት የለፉበትን እርሻ ትተው ወደ ጦርነት ዘመቻው ሲያቀኑ፣ ባለቤታቸው እርሻውን በሽቦና በእንጨት ቢያሳጥሩትም ከሄዱበት ዘመቻ ሲመለሱ አጥሩ ተነቃቅሎ እንደነበር ተናግረዋል፡፡ ‹‹ስመለስ እርሻው ተበልቶ ሳየው አዝኛለሁ›› የሚሉት አቶ እንደራስ የአከባቢው ሰዎች ስንዴ እርሻቸውን ቢሰበስቡላቸውም የጤፍ እርሻቸውን ሳይታጨድ ሰንብቷል፡፡ ‹‹አማራጭ ስላልነበረኝ አጫጆችን ለመቅጠር አስቤ ነበር›› ያሉት አርሶ አደሩ፣ ለዚህም በቀን እስከ 3,000 ሺሕ ብር ያወጡ እንደነበር እንስተዋል፡፡ በመንግሥት ደረጃ የተጀመረው የዘማች አርሶ አደሮችን ሰብል የመሰብሰብ ሥራ ከዚህ ወጪ ታድጓቸዋል፡፡ ታኅሳስ 25 ቀን 2014 ዓ.ም. ወደ አከባቢው ያቀኑት የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች ባለሥልጣን ሠራተኞች በአንድ ቀን ውሎ ከአንድ ሄክታር በላይ በሆነ መሬት ላይ የበቀለውን ሰብላቸውን በመሰብሰብ ረድተዋቸዋል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...