Thursday, December 7, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ስፖርትየወጣት ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከታንዛኒያ ጋር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ዓርብ ይጫወታል

የወጣት ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ከታንዛኒያ ጋር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም ዓርብ ይጫወታል

ቀን:

የደቡብ አሜሪካዋ ኮስታሪካ ዘንድሮ ለምታስተናግደው ዕድሜያቸው ከ20 ዓመት በታች ሴቶች የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ማጣሪያውን እያደረገ የሚገኘው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ሴቶች ብሔራዊ ቡድን፣ የፊታችን ዓርብ ጥር 27 ቀን 2014 ዓ.ም.  ከታንዛኒያ አቻው ጋር በአበበ ቢቂላ ስታዲየም የሚያደርጉት የመልስ ጨዋታ ይጠበቃል፡፡ ታንዛኒያ ባለፈው እሑድ በሜዳው ባደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያን 1 ለ 0 በሆነ ጠባብ ውጤት ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

በአሠልጣኝ ፍሬው ኃይለ ገብርኤል የሚሠለጥነው ብሔራዊ ቡድኑ፣ እስካሁን ባደረጋቸው አራት የደርሶ መልስ የማጣሪያ ጨዋታዎች በታንዛኒያ አቻው ከደረሰበት ሽንፈት በስተቀር ሦስቱን የደርሶ መልስ ጨዋታዎች በአሸናፊነት አጠናቋል፡፡

የመልሱን ጨዋታ ውጤቱን መገልበጥ የሚችል ከሆነ፣ ምናልባትም ለኮስታሪካው ከ20 ዓመት በታች የሴቶች የዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ወደ መጨረሻው ምዕራፍ ይሸጋገራል፡፡

የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን የቡድኑን ዝግጅት አስመልክቶ በማኅበራዊ ትስስር ገጹ እንዳስታወቀው ከሆነ፣ ቡድኑ ከታንዛኒያ እንደተመለሰ ከአንድ ቀን ዕረፍት በኋላ በካፍ የልህቀት ማዕከል ልምምዱን አጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል፡፡ ምክንያቱም ቡድኑ እስካሁን ባደረጋቸው ሦስት ማጣሪያ የደርሶ መልስ ጨዋታዎች ላይ በፍፁም ብልጫ ተጋጣሚዎቹን በሰፊ ውጤት ማሸነፍ የቻለው ጠንካራ ዝግጅት በማድረጉ እንደሆነና ውጤቱም የጠንካራ ዝግጅት ነጸብራቅ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

ታዋቂው የኤሌክትሮኒክስ ብራንድ አይቴል የስትራቴጂ ለውጥ አካል የሆነውን አዲስ አርማ እና መለዮ ይፋ አደረገ።

በአለማችን ታዋቂ ከሆኑት የኤሌክትሮኒክስ ብራንዶች መካከል አንዱ የሆነው እና...

የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ጥሪ ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ

ለሸገር አነስተኛ የፋይናንስ ተቋም አ.ማ ባለአክሲዮኖች በሙሉ የሸገር አነስተኛ የፋይናንስ...

[የክቡር ሚኒስትሩ ጸሐፊ፣ የሌላ ሚኒስትር ጸሐፊ ከሆነችው የቅርብ ወዳጇ ጋር በስልክ እየተጨዋወቱ ነው]

አንቺ ግን ምን ሆነሽ ነው? ጠፋሁ አይደል? ጠፋሁ ብቻ?! ምን ላድርግ ብለሽ...

በሱዳን ላይ ያጠላው የመከፋፈል ዕጣና ቀጣናዊ ተፅዕኖው

የሱዳን ጦርነት ስምንተኛ ወሩን እያገባደደ ይገኛል፡፡ ጄኔራል አብዱልፈታህ አልቡርሃን...