Tuesday, November 28, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

በብረታ  ብረት ምርት ዘርፍ 73 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያላቸው ኩባንያዎች ተሰማርተዋል ተባለ

ተዛማጅ ፅሁፎች

ባለፉት ስድስት ወራት 73 ቢሊዮን ብር ካፒታል ያላቸው አገር በቀል ኩባንያዎች በብረታ ብረት ምርት ዘርፍ መሰማራታቸውን፣ የብረታ ብረት ልማት ኢንስቲትዩት አስታወቀ

ኩባንያዎቹ በስድስት ወራት ውስጥ ወደ ብረታ ብረት ማምረት ዘርፍ የተቀላቀሉ መሆናቸውን፣ የፋብሪካ ግንባታ መጀመራቸውንና በሚቀጥሉት ጥቂት መታት ውስጥ ወደ ምርት እንደሚገቡ በብረታ ብረት ልማት ኢንስቲትዩት የዕቅድ፣ ፖሊሲ ጥናትና መረጃ ዋና ዳይሬክተር አቶ ጥላሁን ባይ ገልጸል።

ወደ ምርት በሚገቡበት ወቅትም ኩባንያዎቹ በዓመት ከ800 ሺሕ ቶን በላይ የተለያዩ የብረታ ብረት ምርቶችን ማምረት እንደሚችሉ አስረድተዋል። ዘርፉን የተቀላቀሉት 11 ኩባንያዎች እንደሆኑ፣ ከ700 ሺሕ ቶን በላይ በዓመት የሚያመርቱት ሰባት ፋብሪካዎች መረታዊ ብረታ ብረት የሚያመርቱ መሆናቸውን፣ እንዲሁም ስቱ በማሽነሪ አንድ ደግሞ በኤሌክትሮኒክስ ዘርፍ የሚሰማሩ እንደሆኑ ገልዋል።

ወደ ዘርፉ የተቀላቀሉት ሁሉም ኩባንያዎች ገር በቀል መሆናቸውን የገለጹት አቶ ጥላሁን በተለይ ከውጭ የሚመጣን ከፍተኛ መጠን ያለው የብረታ ብረት ምርት ለመቀነስ እንደሚረዳ ጠቁመዋል። በገር አቀፍ ደረጃ በዓመት ጥቅም ላይ እየዋለ የሚገኘው የብረታ ብረት ምርት ከአሥር ሚሊን ቶን በላይ እንደሚሆን ከዚህም ቢያንስ 70 በመቶ የሚሆነውን በገር ውስጥ ለመሸፈን እየተራ እንደሚገኝ አክለዋል።

የብረታ ብረት ፋብሪካዎች በተለይ የግዓት አቅርቦትና የውጭ ምንዛ እጥረት ትልቁ ፈተናቸው መሆኑን የገለት አቶ ጥላሁን ፋብሪካዎቹ ማምረት ከሚችሉት በአማካይ 17 በመቶ ባልበለጠ አቅማቸው እንደሚሩም ተናግረዋል።

ይህንን ችግር ለመቅረፍም የገር ውስጥ ብረትን በግብዓትነት መጠቀም እንዲቻል በየቤቱ ከሚሰበሰቡት በተጨማሪ በመንግት ተቋማት የሚገኙ ቁርጥራጭ ብረቶችን ወደ ማቅለጫ በማስገባት ለፋብሪካዎቹ ለማቅረብ መታቀዱን ገልጸዋል።

አሁን ወደ ዘርፉ የተቀላቀሉትን ጨምሮ የብረታ ብረት ልማት ኢንስቲትዩት 28 ፋብሪካዎች የቴክኒክ ድጋፍ እንደሚያደርግ ምርት ያቆሙትም ወደ ምርት እንዲመለሱ እየራ መሆኑን አቶ ጥላሁን ገልጸዋል።

በዚህም መረት ባለፉት ስድስት ወራት በመለዋወጫ እጥረትና ሌሎች ምክንያቶች ማምረት አቁመው የነበሩ ስምንት ፋብሪካዎች ወደ ምርት መግባታቸው ተገልጿል። ፋብሪካዎቹ መታዊ የማምረት አቅማቸው ከ619 ሺሕ ቶን በላይ እንደሆነ፣ 615 ሺሕ ቶን የሚሆነው መረታዊ ብረታ ብረት እንዲሁም ቀሪው በማሽነሪና ኤሌክትሮኒክስ ዘርፎች ላይ የተሰማሩ ፋብሪካዎች የሚያመርቱት እንደሆነ አቶ ጥላሁን አብራርተዋል።

በኢትዮጵያ በየመቱ የብረታ ብረት ምርትን ለማስገባት አሥር ቢሊዮን ዶላር የሚጠጋ ገንዘብ የሚወጣ ሲሆንገር ውስጥ የሚመረተው ከውጭ ከሚመጣው ጋር ሲነፃፀር ከአምስት በመቶ እንደማይበልጥ የኢንስቲትዩቱ መረጃ ያሳያል።

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች