Wednesday, October 4, 2023
- ማስታወቂያ -
- ማስታወቂያ -

ከውጭ የሚመጡ የጨርቃ ጨርቅ ምርቶችን በአገር ውስጥ ለመተካት ለዘርፉ የቅድሚያ ቅድሚያ መሰጠቱ ተገለጸ

ተዛማጅ ፅሁፎች

ከውጭ የሚመጡ የጨርቃ ጨርቅ ምርቶችን በገር ውስጥ ለመተካት ለዘርፉ በገንዘብ አቅርቦት የቅድሚያ ቅድሚያ መሰጠቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር አስታወቀ።

ይህ የተገለጸው የኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ከአገር መከላከያ ሠራዊት፣ ከፌዴራልና ከክልል ፀጥታ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች፣ እንዲሁም ዘርፉ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የደንብ ልብስና ተያያዥ ምርቶችን በአገር ውስጥማምረት፣ አቅም መፍጠር በሚያስችል ፕሮጀክት ላይ ማክሰኞ የካቲት 8 ቀን 2014 ዓ.ም. ውይይት ባደረገበት ወቅት ነው፡፡

ፕሮጀክቱ ከዚህ ቀደም ከተጀመረው የተማሪዎች ጫማና ቦርሳን በገር ውስጥ የማምረት ፕሮጀክት ጋር ተመሳሳይነት ያለው መሆኑን፣ በፀጥታ ይሎች የደንብ ልብስ በኩልም ከፍተኛ የገበያ ድል በመኖሩ ትኩረት መደረጉን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል ገልጸዋል።

በተለይ የጥታ ይሎች አልባሳትና ጫማዎች የደንነት ጋት እንዳይኖርባቸውገር ውስጥ እንዲመረቱ የሚያስችል እንደሆነም አቶ መላኩ አክለዋል። ካለው አቅም አንር ከገር ውስጥ አልፎ ለጎረቤት ሮች መላክን ታሳቢ ያደረገ ፕሮጀክት መሆኑን ገልጸዋል።

ከዚህ በፊት በተጀመረው የተማሪዎች ጫማና ቦርሳን በገር ውስጥ የመተካት ፕሮጀክት በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ከ718 ሺ በላይ ጥንድ ጫማዎች መቅረቡን ገልጸውከአንድ ሚሊን በላይ ጫማዎች ደግሞ ለመከላከያራዊት፣ ለፌራል ፖሊና ለክልል ፖሊሶች ከገር ውስጥ አምራቾች ቀርበዋል ብለዋል።

የአርባ ምንጭ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ የሽያጭ ክፍል ላፊ አቶ አብዱራህማን ከማል ዘርፉ ከፍተ ካፒታልና የራ ማስኬጃ የሚፈልግ በመሆኑ በተለይ የገንዘብ አቅርቦት ከፍተኛ ችግር እንደሆነ ገልጸዋል። ዘርፉ ካለው አቅም አንድገቱ ዝቅተኛ መሆኑን ጠቁመው፣ በተለይ መንግት የገበያ ትስስን በመፍጠር ድጋፍ ያደር ይገባል ብለዋል።

ፋብሪካዎች በተለያዩ ችግሮች ምክንያት ከአቅማቸው በታች እያመረቱ የሚኙት በውጭ ምንዛ እጥረት በብድር አቅርቦት ችግር መሆኑን ገልጸው በተለይ የኢትዮጵያ ልማት ባንክና የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ትኩረት ሰጥተው ለመራት መስማማታቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ጨርቃ ጨርቅ አምራቾች ማኅበር የቦርድ አባልና የዕድገት ጋርመንት ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ብርሃኑ ደገፉ ደግሞ ለአምራቾቹ የሚሰጡ ጥቅማ ጥቅሞቹ ከውጭ ከሚመጡ ኢንቨስተሮች ያነሰ በመሆኑ፣ ተወዳዳሪ መሆን አለመቻሉን ይገልጻሉ። የምርቶቹ የጥራት ችግር በጥሬ ዕቃ እጥረት የሚከሰት በመሆኑ የገንዘብ አቅርቦቱን በማሻሻል፣ በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ ተወዳዳሪ የሆነ ምርት እንዲመረት ድጋፍ ሊደረግ ይገባል ብለዋል።

ዘርፉ ከገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ከሌሎች ድርጅቶች ጋር የሚወዳደር ስለሆነ የተለየ ድጋፍ ሊደረግ እንደሚገባ ገልጸው ለዚህም ካለው ውስን ብት ላይ የቅድሚያ ቅድሚያ እንዲሰጠው ፕሮጀክቱ እንደሚያግዝ አስረድተዋል

ገር ውስጥ የሚመረቱ ምርቶችን የጥራት ችግር በተለይ በጨርቃ ጨርቅ በኩል በቀለም፣ ጨርቅ ይነትና መሰል የጥሬ ቃ ችግሮች እንዲሁም በጫማ ላይ ደግሞ በሶልና በማስቲሽ ጥራት ችግሮች የሚከሰት በመሆኑ ፕሮጀክቱ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል ብለዋል። 

በአጠቃላይ በጨርቃ ጨርቅ ዘርፉ በመት ወደ ውጭ የሚላከው ምርት በአማካ114 ሚሊን ዶላር መሆኑን፣ ከውጭ የሚመጣው መታዊ አማካ ምርት ደግሞ 545 ሚሊን ዶላር መሆኑን አቶ መላኩ ጠቁመዋል። በኢትዮጵያ በአቃላይ ከ1‚700 በላይ ጥቃቅን አነስተኛና መካከለኛ እንዲሁም ከ200 በላይ ከፍተኛ የጨርቃ ጨርቅ አምራች ኢንዱስትሪዎች ቢኖሩም በሙሉ አቅማቸው እያመረቱ ባለመሆናቸው በገቢና ወጪ ምርካከል ልዩነቱ ከፍ ማለቱን ገልጸዋል። 

 

spot_img
- Advertisement -spot_img

የ ጋዜጠኛው ሌሎች ፅሁፎች

- ማስታወቂያ -

በብዛት ከተነበቡ ፅሁፎች