Friday, March 24, 2023
- Advertisment -
- Advertisment -

[ድርድር የሚባል ነገር ፈጽሞ አይታሰብም በማለት በተደጋጋሚ ለሚዲያ ሲገልጹ የነበሩት ክቡር ሚኒስትሩ፣ የፖለቲካ አማካሪያቸውን ቢሮ አስጠርተው ምክክር እያደረጉ ነው]

  • ክቡር ሚኒስትር በአስቸኳይ እንደፈለጉኝ ሰማሁ፣ ምን ገጠመዎት?
  • ጎሽ እንኳን ቶሎ መጣህ፡፡
  • በሰላም ነው?
  • ምን ሰላም አለ ብለህ ነው?
  • ምን ገጠመዎት?
  • በሉ ተባለ እኔም ፈጽሞ የሚታሰብ ነገር እንዳልሆነ ተናገርኩ… አሁን በድንገት ተነስተው ሌላ ይላሉ፡፡
  • አልገባኝም ክቡር ሚኒስትር? ፈጽሞ አይታሰብም ያሉት ምንድነው? 
  • ድርድር ነዋ፡፡ 
  • የግድቡን ድርድር ማለትዎ ነው?
  • ወዴት ነው የምትሄደው አንተ ደግሞ? 
  • ድርድር ከሆነ የሚሆነው የህዳሴ ግድቡ ድርድር ይሆናል ብዬ ነው… ስላልገባኝም ነው?
  • እዚህ የአገር ውስጥ ነው… የሰሜኑ ድርድር ነው እንጂ፡፡
  • እሱንማ በሚገባ ሲያስረዱ አልነበረም እንዴ? እንዲያውም ሰሞኑን የተናገሩትን ብዙ ሰዎች ሲቀባበሉት አይቻለሁ። 
  • ምን ብዬ የተናገርኩትን ነው የተቀባበሉት?
  • አሸባሪ ተብሎ ከተፈረጀ ድርጅት ጋር ፈጽሞ ድርድር አይኖርም፣ አይታሰብም ያሉትን፡፡ 
  • ይኸውልህ… እሱን እኮ ነው የምልህ፣ እኛን እንደዚያ በሉ ይላሉ ውሎ ሳያድርና የተናገርነውን ሳያዘጋጁን ሐሳብ ይቀይራሉ፣ ታዲያ ቃል አባይ እንጂ እንዴት ሰላም ልሆን እችላለሁ?
  • ድርድር ይደረጋል ተባለ እንዴ?
  • የት ነበርክ አንተ ደግሞ…?
  • አልሰማሁም ክቡር ሚኒስትር። 
  • ተባለ እንጂ… ለዚያውም መላው ሕዝብ እንዲያውቀው ተደርጎ ነው የተገለጸው፡፡
  • እርስዎ ለምን ተጨነቁ ታዲያ?
  • ምን ይላል ይኼ? ድርድር ፈጽሞ አይታሰብም ብዬ ስናገር ነበር እያልኩህ? ወዳጆቻችን ቢጠይቁ ምን እመልሳለሁ አሁን?
  • መንግሥት በይፋ የገለጸውን ነገር ወዳጆቻችን ምን ብለው ሊጠይቁ ይችላሉ?
  • አሸባሪ ተብሎ ከተፈረጀ ድርጅት ጋር በጭራሽ ድርድር አይኖርም ያልከው ከምን ተነስተህ ብለው መጠየቃቸው አይቀርም። 
  • እንደዚያ ማለትዎ ነው ያሳሰበዎት?
  • እንዴት አያሳስበኝም? አስረግጬ እኮ ነው የተናገርኩት፡፡
  • ይህ ብዙ አያሳስብም… መፍትሔ አለው፡፡
  • ምን ዓይነት መፍትሔ? ብዙ ታለፋኛለህ እንጂ ብልህ እኮ ነህ?
  • መፍትሔው ቀላል ነው፡፡
  • እኮ ምንድነው?
  • የተናገሩትን ደግመው መናገር ነው። 
  • ምን እያልክ ነው?
  • አሸባሪ ተብሎ ከተፈረጀ ድርጅት ጋር ፈጽሞ ድርድር አይኖርም፣ አይታሰብም ይበሉ፡፡
  • ጤነኛ አይደለህም እንዴ?
  • ክቡር ሚኒስትር አያስቡ መፍትሔው እሱ ብቻ ነው፡፡
  • እንዴት?
  • ምክንያቱም መንግሥት ወደ ድርድር ሊገባ የሚችለው ይህንን የሕግ ግዴታ ካነሳ ብቻ ነው። 
  • አልገባኝም?
  • ይኸውልዎት ክቡር ሚኒስትር መንግሥት ብድግ ብሎ ወደ ድርድር ሊገባ አይችልም፣ ወደ ድርድር የሚገባ ከሆነ አስቀድሞ ፍረጃውን ማንሳቱ አይቀርም።
  • እህ… ድርድር ከመጀመሩ በፊት ፓርላማው የአሸባሪነት ፍረጃውን እንዲያነሳ ይደረጋል እያልክ ነው?
  • በትክክል፡፡
  • ስለዚህ እኔ የተሳሳትኩት ነገር የለም ማለት ነው? እንደዚያ ማለትህ ነው አይደል?
  • ልክ ነዎት፣ እርስዎ ሽብርተኛ ከተባለ ድርጅት ጋር ድርድር አይኖርም አይደለም እንዴ ያሉት?
  • አዎ፡፡
  • ስለዚህ ድርድሩ ከመጀመሩ በፊት ፍረጃው ስለሚነሳ እርስዎ የተናገሩት ትክክል ነው ማለት ነው። 
  • አሃ… ድርድሩ ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር አይሆንም ማለት ነው? እንደዚያ ነው አይደል?
  • በትክክል፡፡
  • አንተ ዘንድ መላ አይጠፋም የምለው ለዚህ ነው… ግን…
  • ግን ምን ክቡር ሚኒስትር?
  • ግን በምን እርግጠኛ መሆን ይቻላል?
  • ምኑ ላይ?
  • ፍረጃው ሳይነሳ ድርድር ቢካሄድስ? 
  • እንደዚያ ሊሆን አይችልም፣ ከሆነም ደግሞ…
  • እሺ… ከሆነ ደግሞ ምን?
  • ከሆነማ ችግሩ የእርስዎ ብቻ ሳይሆን የመንግሥትም ይሆናል፣ ስለዚህ መንግሥት ፈጽሞ እንደዚያ አያደርግም፡፡
  • እንደዚያ አይደለም ማለት ያለብህ!
  • እንዴት ልበል?
  • መንግሥት ፈጽሞ ከሽብርተኛ ጋር አይደራደርም!

[ክቡር ሚኒስትሩ አመሻሹን ወደ መኖሪያ ቤታቸው ሲገቡ ባለቤታቸው በቴሌቪዥን እየተላለፈ ያለውን ውይይት በተመስጦ እየተከታተሉ አገኟቸው]

  • እንዴ መንግሥት ወሰነ በቃ?
  • በፍጹም፡፡ 
  • ይኸው አሁን የተባለውን አዳመጥኩት እኮ?
  • ፈጽሞ ከሽብርተኛ ድርጅት ጋር ድርድር አይደረግም፡፡
  • አዬ… እኔ ስለእሱ አይደለም የጠየኩህ፣ የመንግሥት ተቋማት በምርመራ ጋዜጠኞች ይመረመራሉ የተባለውን ነው የምልህ።
  • እንደዚያ ተብሏል እንዴ?
  • ከዚህ በኋላ በመንግሥት ሚዲያዎች የምርምራ ጋዜጠኝነት እንደሚጀመርና የመንግሥት ተቋማት ጉድ እንደሚገለጥ ሲናገሩ ሰምቻለሁ፡፡ 
  • እሱን እንኳ ተይው፡፡
  • እንዴት? 
  • ጋዜጠኞች ይችሉታል ብለሽ ነው?
  • እንዴት አይችሉትም? 
  • ያስቸገረውን ጋዜጠኛ አንዱ ክልል ወስዶ ሲያስረው ይቆማል። 
  • የመንግሥት ድጋፍ ስለሚኖራቸው ለማሰር ይቸገራሉ፣ እሳቸውም ባለሥልጣናት በራቸውን ለምርመራ ጋዜጠኞች ክፍት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
  • ጋዜጠኛን ለማሰር እንኳን ችግር የለውም… በተለመደው መንገድ በቀላሉ ማሰር ይቻላል።
  • እንዴት ተደርጎ? በምን ምክንያት?
  • በዘገባው የአንድን ማኅበረሰብ ክብር ነክቷል ብሎ ከአዲስ አበባ ውጪ ማሰር ይቻላል። 
  • ያላደረገውን?
  • እሱን ፍርድ ቤት ይወስነዋል። 
  • ምንም ችግር አይከሰትም በለኛ?
  • አልኩሽ እኮ፣ እንኳን ጋዜጠኛ ዋናውም አልቻሉትም፡፡
  • ዋናው ማናቸው? 
  • ኦዲተሩ!

በብዛት የተነበቡ ፅሁፎች

አሜሪካ ሕወሓትን በማሳመንና በመጫን በሰላም ሒደቱ ትልቅ ሚና መጫወቷን የኢትዮጵያ ዋና ተደራዳሪ አስታወቁ

የተመድና የአውሮፓ ኅብረት አበርክቶ አሉታዊ እንደነበር ጠቁመዋል በመንግሥትና በሕወሓት መካከል...

አገር የሚገቡ የግል ዕቃዎችን በሚገድበው መመርያ ምክንያት በርካታ ንብረቶች በጉምሩክ መያዛቸው ተገለጸ

በአየር መንገድ ተጓዦች ወደ አገር የሚገቡትን የግል መገልገያ ዕቃዎች...

ብሔራዊ ባንክ ለጥቃቅንና አነስተኛ ብድሮች ዋስትና መስጠት ሊጀምር ነው

ኢንተርፕራይዞችን ብቻ የሚያገለግል የፋይናንስ ማዕከል ሥራ ጀመረ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ...

አዋሽ ባንክ ለሁሉም ኅብረተሰብ የብድር አገልግሎት የሚያስገኙ ሁለት ክሬዲት ካርዶች ይፋ አደረገ

አዋሽ ባንክ ለሁሉም የኅብረተሰብ ክፍሎች በዘመናዊ መንገድ ብድር ማስገኘት...
- Advertisment -

ትኩስ ፅሁፎች

ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አቶ ጌታቸው ረዳን የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር አድርገው ሾሙ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር) አቶ ጌታቸው ረዳ የትግራይ ክልል...

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...
spot_img

ተዛማጅ ፅሁፎች

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር ሚኒስትር? እርሶዎማ ቀጠሮ መያዝ አያስፈልግዎትም። ምን ገጠመዎት? እኔማ ምን ይገጥመኛል፣ አንተኑ ልጠይቅህ እንጂ? ምን? እውነት ለመናገር የማየው ነገር አሳስቦኛል። ይንገሩኝ...

[የባለሥልጣኑ ኃላፊ የቴሌኮም ኩባንያዎች የስልክ ቀፎ የመሸጥ ፈቃድ እንዳላቸው ለማረጋገጥ ክቡር ሚኒስትሩ ጋር ደወሉ]

ክቡር ሚኒስትር ዕርምጃ ከመውሰዳችን በፊት አንድ ነገር ለማጣራት ብዬ ነው የደወልኩት። እሺ ምንን በተመለከተ ነው? የቴሌኮም ኩባንያዎችን በተመለከተ ነው። የቴሌኮም ኩባንያዎች ምን? የቴሌኮም ኩባንያዎች የሞባይል ቀፎ እንዲሸጡ በሕግ...

[ክቡር ሚኒስትሩ ተቋቋመ ስለተባለው የሽግግር መንግሥት ከአማካሪያቸው መረጃ እየጠየቁ ነው]

እኛ ሳንፈቅድ እንዴት ሊያቋቁሙ ቻሉ? ስምምነታችን እንደዚያ ነው እንዴ? በስምምነታችን መሠረትማ እኛ ሳንፈቅድ መቋቋም አይችልም። የእኛ ተወካዮችም በአባልነት መካተት አለባቸው። ታዲያ ምን እያደረገ ነው? ስምምነቱን መጣሳቸው...