Monday, December 4, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ማኅበራዊኢትዮጵያዊነት የአገራዊ ምክክሩ ቀዳሚ አጀንዳ እንዲሆን ተጠየቀ

ኢትዮጵያዊነት የአገራዊ ምክክሩ ቀዳሚ አጀንዳ እንዲሆን ተጠየቀ

ቀን:

ኢትዮጵያዊነት የገራዊ ምክክሩ ቀዳሚ አጀንዳ እንዲሆን ኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ድርጅት ጠየቀ።

ኢትዮጵያዊነት የዜጎች ብት ማስከበሪያ ድርጅት ከመስከረም 2013 ዓ.. ጀምሮ በዜጎች መብቶችና በሕዝባዊ አንድነት ላይ ትኩረት አድርጎ የሚራ የሲቪክ ማበር ሲሆን፣ ቅዳሜ መጋቢት 3 ቀን 2014 ዓ.. የሚያካሂደውን የመተዋወቂያ ፕሮግራም አስመልክቶ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

በመግለው ላይ የተገኙት የድርጅቱ ራ አስኪያጅ አቶ ሞገስ በቀለ በተለይ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ኢትዮጵያዊነት የሚለው አጀንዳ በአገራዊ ምክክሩ ውስጥ በቀዳሚነት ሊነሳ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡ ይህንንም የሚጠይቅ ደብዳቤ በመጪው ሳምንት ለአገራዊ ምክክር ኮሚሽኑ እንደሚያስገቡ ተናግረዋል።

ገራዊ ምክክሩ በተለይ በኢትዮጵያዊነት ላይ ተመሳሳይ አመለካከት ከተያዘና ስምምነት ላይ ከተደረሰ በኋላ፣ ወደ ሌሎች ጉዳዮች መሄድ አለበት ብለዋል። ኢትዮጵያዊነት የሚለውን ሐሳብ የማይቀበል አካል ባለበት ሁኔታ፣ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ምክክር ቢደረግ ውጤት አያመጣም ሉም አስረድተዋል።

መንግትን በተመለከተ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈረው ግጭትና አለመግባባት ምክንያት የሆኑ የ መንግቱ አንቀጾች ተለይተው ግልጽ ውይይት ሊደረግባቸው ይገባል ብለዋል። መሻሻል ያለባቸው አንቀጾችም በቀጣይ የችግር ምንጭ እንዳይሆኑ በማድረግ ማሻሻል ያስፈልጋል ብለዋል።

ምክክሩ የሁሉም ብረተሰብ እንዲሆንና በተለይ በምሁራንና በፓርቲዎች ላይ ብቻ የተንጠለጠለ መሆን እንደሌለበት አሳስበው፣ በማኅበረሰቡ ውስጥ ያሉ ሁሉም አካላት ሊወከሉ ይገባል ብለዋል፡፡

‹‹ለምክክር ኮሚሽኑ ከተጠቆሙት የመጀመሪያ 632 ሰዎች ውስጥ ከ200 በላይ የሚሆኑት በእኛ ድርጅት አማካነት የተጠቆሙ ናቸው፤›› ያሉት አቶ ሞገስ፣ ከጥቆማው ባለፈ ሁሉም ብረተሰብ በምክክሩ ላይ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያዊነት ሴቶችን ማስተማር፣ የኢትዮጵያ ዝብን አንድነት ማጠናከርና የዜግነት ልቦናን ማዳበር ላይ ትኩረት አድርጎ የሚራው ኢትዮጵያዊነት የዜጎች መብት ማስከበሪያ ድርጅት በ1984 ዓ.ም. እነ ዶ/ር ሀዲስ ለማየሁ፣ ሌተና ጄኔራል ጃጋማ ኬሎና ሌሎችም በጋራ መርተውት የነበረውን ‹‹የኢትዮጵያዊነት ማበር›› ሐሳቦች መነሻ በማድረግ በ2013 ዓ.ም. የተመሠረተ ድርጅት እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

በዓለም አቀፍ ደረጃ ሕይወታቸውን በኤድስ ምክንያት ላጡ ሰዎች 35ኛ ዓመት መታሰቢያ

ያለፍንበትን እያስታወስን በቁርጠኝነት ወደፊት እንጓዝ - በኧርቪን ጄ ማሲንጋ (አምባሳደር) በየዓመቱ...

እዚያ ድሮን… እዚህ ድሮን…

በዳንኤል ካሳሁን (ዶ/ር) ተዓምራዊው የማዕበል ቅልበሳ “በሕግ ማስከበር” ዘመቻው “በቃ የተበተነ...

ለፈርጀ ብዙ የማንነት ንቃተ ህሊናችን የሚጠቅሙ ጥቂት ፍሬ ነገሮች

በበቀለ ሹሜ ከጨቅላነት ጅምሮ ያለ የእያንዳንዳችን የሰብዕና አገነባብ ከቤተሰብ እስከ...