Wednesday, March 22, 2023
- Advertisement -
- Advertisement -
ዜናየሶማሌ ፕሪንቲንግ ፕሬስ ባለቤት በፅኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ ውሳኔ ተሰጠ

የሶማሌ ፕሪንቲንግ ፕሬስ ባለቤት በፅኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ ውሳኔ ተሰጠ

ቀን:

በሙስና ወንጀል ተከሰው የነበሩት የሶማሌ ፕሪንቲንግ ፕሬስ ባለቤት አቶ ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ)ን ጨምሮ አራት ግለሰቦች፣ በፅኑ እስራትና በገንዘብ እንዲቀጡ፣ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሦስተኛ የሙስና ወንጀሎች ችሎት መጋቢት 5 ቀን 2014 ዓ.ም. ውሳኔ ሰጠ፡፡

ተከሳሾቹ ቅጣቱ የተወሰነባቸው ከክልሉ ተማሪዎች መጻሕፍትትመት ጋር በተያያዘ ያላግባብ ፈጽመዋል በተባሉበት ከባድ የሙስና ወንጀል ነው፡፡ ተከሳሾቹ የወንጀል አንቀጽ 32(1 ሀ እና )፣33 እና የሙስና ወንጀል አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀጽ 13(1 እና (3)ን በመተላለፍ በቀረበባቸው በከባድ የሙስና ወንጀል፣ ዓቃቤ የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን በማቅረብ እንደ ክሱ በማስረዳቱ ጥፋተኛ መባላቸውን ፍርድ ቤቱ በውሳኔው ላይ በዝርዝር አስቀምጧል፡፡ ተከሳሾቹምመከላከያ ማስረጃዎቻቸውን ያቀረቡ ቢሆንም፣ የዓቃቤ ሕግን ማስረጃዎች ማስተባበል ባለመቻላቸው ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ እንዳላቸውም ውሳኔው ያስረዳል፡፡

የክርክር ሒደቱን የመረመረው ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች አንደ ተሳትፎ ደረጃቸው በተከሰሱበት አንቀጽ ወንጀሉን ስለመፈጸማቸው በማስረጃ በመረጋገጡ፣  የቀድሞ የኒያላ ኢንሹራንስ አክሲዮን ማኅበር ጅግጅጋ ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ የነበሩት አቶ አብዲ የሱፍ መሐመድ ማኅበራዊላፊነትመወጣታቸው፣ የወንጀል ሪከርድ የሌለባቸው በመሆኑ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪመሆናቸው፣ የጤና እክል ስላጋጠማቸውና አገራዊ ልማት ተሳትፎ እንዳደረጉ ጠቅሰው ካቀረቧቸው አጠቃላይ 11 የቅጣት ማቅለያዎች መካከል ሰባቱን በማቅለያነት በመያዝ አምስት ዓመታት ፅኑ እስራትና 5,500 ብር እንዲቀጡ ወስኗል፡፡

የሶማሌ ፕሪንቲንግ ፕሬስ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) ካቀረቧቸው ስምንት የቅጣት ማቅለያዎች ውስጥ ስድስቱን በመያዝ ስድስት ዓመትስራትና 8,000 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ የተወሰነ ሲሆን፣ ሌሎቹ ሁለት ተከሳሾች የቀድሞው የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ መሐመድ አህመድና አቶ አብዱላሂ ሁሴን ደግሞ በሌሉበት የተከሰሱ በመሆናቸው፣ እያንዳንዳቸው ስምንት ዓመት ፅኑ እስራትና 30,000 ብር የገንዘብ ቅጣት እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡ የፌዴራል ፖሊስም በሌሉበት ውሳኔ የተሰጠባቸውን ፍርደኞች አፈላልጎ ለማረሚያ ቤት እንዲያስረከብና ማረሚያ ቤቱም እስራቱን አንዲያስፈጽም ትዕዛዝ በመስጠት መዝገቡን ዘግቷል።

የሶማሌ ክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊ የነበሩት አቶ መሐመድ አህመድ መጋቢት 7 ቀን 2010 .ም. ከሶማሌ ፕሪንቲንግ ፕሬስ ባለቤትና ሥራ አስኪያጅ አቶ ቴዎድሮስ አዲሱ (ቴዲ ማንጁስ) ጋር ለመጀመሪያናሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች መጻሕፍት አሳትሞ የማቅረብ የግዥ ውል ጋር በተያያዘ፣ ተከሳሹ የፌዴራል መንግሥት የተመዘገበ ሕዝባዊ ድርጅትኒያላ ኢንሹራንስ አሠራርና መመርያ ውጪ ያለአግባብና ባልተገባ የውል ስምምነት፣ መጽሐፉ ታትሞ ገቢ ሳይደረግ ለአቶ ቴዎድሮስ (ቴዲ ማንጁስ) 15‚306‚803 ብር ክፍያ እንዲከፈል ማድረጋቸውን ዓቃቤ ሕግ በክሱ አስፍሯል፡፡ በሌሉበት የተፈረደባቸው ተከሳሾችም ገንዘቡ እንዲመለስ ወይም መጻሕፍቱ እንዲገቡ ባለማድረጋቸው፣ አቶ ቴዎድሮስ ደግሞ ከመንግሥትና ሕዝባዊ ድርጅት ኃላፊዎች ጋር ተመሳጥረው ያላግባብ ዋስትና እንዲሰጣቸው አድርገው ክፍያ በመውሰድ፣ መጻሕፍቱንም ባለማቅረባቸው፣ በሕዝብና በመንግሥት ገንዘብና በመማር ማስተማርደት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደረሱ መሆናቸውን በመዘርዘር ዓቃቤ ሕግ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ መሆናቸውን ገልጾ ክስ እንደ ተመሠረተባቸው መዘገባችን ይታወሳል፡፡

spot_img
- Advertisement -

ይመዝገቡ

spot_img

ተዛማጅ ጽሑፎች
ተዛማጅ

[ክቡር ሚኒስትሩ ከሚያከብሯቸው አንድ የቀድሞ ጉምቱ ፖለቲከኛ ስልክ ተደውሎላቸው እያወሩ ነው]

አንዳንድ ነገሮች ቢያሳስቡኝ ነው ቀጠሮ ሳልይዝ ላወራህ የፈለኩት ክቡር...

የትግራይ ክልል የሽግግር አስተዳደር ምሥረታና የሰላም ስምምነቱ ሒደት

በትግራይ ክልል ጊዜያዊ የሽግግር መንግሥት ለመመሥረት ደፋ ቀና እየተባለ...

ጥራዝ ነጠቅነት!

ከሜክሲኮ ወደ ጀሞ እየሄድን ነው፡፡ የተሳፈርንበት አሮጌ ሚኒባስ ታክሲ...

አወዛጋቢነቱ የቀጠለው የአዲስ አበባ የጤፍ ገበያ

ሰሞኑን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጤፍ የተከሰተውን የዋጋ ንረት...